የአቶ አስራት ጣሴ የፍርድ ቤት ውሎ – ከዳዊት ሰለሞን (ጋዜጠኛ)

 

አስራት ጣሴ
ዳኛ –የማረሚያ ቤቱ ፖሊስን ‹‹እዚሁ ልትለቃቸው ትችላለህ
የማረሚያ ቤቱ ፖሊስ ‹‹አለቃቸውም››
አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የኢትዮጵያ ቴሌቭዥንና ሬዲዩ ድርጅት ባቀረበው አኬልዳማ በተሰነ ዶክመንተሪ ፊልም ስሜን አጥፍቷል በማለት ያቀረበው የፍትሀ ብሄር ክስ በአስር ቀናት ውስጥ ውሳኔ ማግኘት እንደሚገባው አዋጅ እንደሚደነግግ የተረዱት አቶ አስራት ጣሴ በአዲስ ጉዳይ መጽሔት የፍትህ መጓተት ከፍርድ ቤቱ ፍትህ ማግኘት እንደማይቻል ማሳያ ነው በማለት በመጻፋቸው ፍርድ ቤቱ ዘልፈውኛል በማለት ክስ መስርቶ ለስምንት ቀናት በቂሊንጦና በፖሊስ ጣብያ መታሰራቸው አይዘነጋም፡፡
በዛሬው የከሰዓት በኋላ የፍርድ ቤት ውሎ ዳኛ ቱታ ለብሰውና ነጠላ ጫማ ተጫምተው እጆቻቸው በካቴና ተጠፍሮ በሁለት የታጠቁ የማረሚያ ቤቱ ፖሊሶች የቀረቡት አቶ አስራት የቅጣት ማቅለያ እንዲያቀርቡ ሲጠየቁ ‹‹ምንም አይነት ማቅለያ አላቀርብም››የሚል ምላሽ ሰጥተዋል፡፡
ዳኛዋ ውሳኔውን ለማስደመጥ ተጨማሪ 45 ደቂቃዎችን እንዲጠብቁ በማዘዝ ከአንድ ሰዓት በኋላ የአስራትን ጉዳይ ለማድመጥ የመጡ ሰዎች ወደ ችሎት እንዲገቡ ተደርገዋል፡፡ዳኛዋ ውሳኔውን ከማንበባቸው አስቀድሞ ጋዜጠኞች በችሎቱ መገኘታቸውን በመጠየቅ ‹‹የአዲስ ጉዳይ ወይም የአዲስ ነገር ጋዜጠኛ ናፍቆት የሚባሉ አሉ በማለት ጠየቁ ነገር ግን ናፍቆት ነኝ ያለ ጋዜጠኛ በስፍራው አልተገኘም፡፡ዳኛዋ ቀጠሉ‹‹ለማንኛውም ጋዜጠኞች ፍትሃዊ ዘገባ እንድትሰሩ ትጠየቃላችሁ ታላቁ ህዝብ መረጃ የማግኘት መብት አለው ያልተባለ ነገር በመጻፍ የተሳሳተ መረጃ ማስተላለፍ አይገባም››የሚል ምክር ካስተላለፉ በኋላ ውሳኔውን በንባብ አስደመጡ፡፡

ውሳኔው አቶ አስራት ፍርድ ቤቱን የኢህአዴግ በማለት መሳደባቸውን አግባብ አለመሆኑን በመጥቀስ የአምስት ወራት እስር መወሰኑን ነገር ፍርድ ቤቱ በራሱ የቅጣት ማቅለያ መመዘኛ መሰረት ቅጣቱን በገደብ እንዲሁም በማድረግ በሁለት አመት ገደብ እንዲወጡ ወስኗል››አሉ፡፡
ዳኛዋ አስራትን ላቀረባቸው ፖሊስ ‹‹እዚሁ ልትለቋቸው ትችላላችሁ ››ቢሉም ቆፍጠን ያለው ፖሊስ ለዳኛ‹‹አንለቃቸውም ከማረሚያ ቤት ስለመጡ ከዚያ ነው የሚለቀቁት››የሚል ምላሽ ሰጥቷል፡፡

አንድነት እና መኢአድ ብአዴንን በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ

አንድነት እና መኢአድ ብአዴንን በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲና የመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት ብአዴንን በመቃወም በባህርዳር ከተማ ህዝባዊ የተቃውሞ ሰልፍ ጠሩ፡፡ ፓርቲዎቹ ነገ በ4 ሰዓት በአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት በጋራ መግለጫ እንደሚሰጡ ይጠበቃል፡፡ ለተቃውሞ ሰልፉ አስፈላጊው የማሳወቅ ተግባር መጠናቀቁ ታውቋል፡፡

አንድነትና መኢአድ እሁድ የካቲት 16 ቀን 2006 ዓ.ም የጠሩት የተቃውሞ ሰልፍ መነሻ ምክንያት እንዲያስረዱ በፍኖተ ነፃነት የተጠየቁት የአንድነት ፓርቲ የፖለቲካ ጉዳዮች ኃላፊ አቶ ሰለሞን ስዩም “አማራ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድርና የብአዴን የጽ/ቤት ኃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን የአማራን ህዝብን ክብር የሚያዋርድና በለሌሎች ብሔረሰቦች በክፉ እንዲታይ የሚያደርግ የጥላቻ ንግግር በማድረጋቸውና ብአዴንም እንደ ፓርቲ ማስተባበያም ሆነ የማስተካከያ እርምጃ ባለመውሰዱ የግለሰቡን አቋም እንደሚጋራ ያመለክታል” ብለዋል፡፡

የመኢአድ ም/ፕሬዝደንት አቶ ተስፋዬ መላኩ በበኩላቸው “የአማራ ህዝብን እየመራሁ ነው እያለ እንደዚህ አይነት አስነዋሪ ንግግር ያደረገውን ባለስልጣና የሚወክለውን ፓርቲ ለማውገዝ እንዲሁም ለህግ እንዲቀርብ ለመጠየቅ ነው ሰልፉ የተጠራው” ብለዋል፡፡

የፓርቲዎቹ የባህርዳርና አካባቢዋ መዋቅሮች የተቃውሞ ሰልፉን ለማስተባበር ዝግጅታቸውን ያጠናቀቁ ሲሆን የባህርዳር ከተማና የአካባቢዋ ህዝብ በነቂስ በመውጣት በሰልፉ ተቃውሞውን እንዲገልፅም ጥሪ አቅርበዋል፡

በላይ ዘለቀ ከስብሐት ገብረ እግዚአብሔር-(የካቲት መጽሔት፣ 3ኛ ዓመት ቁጥር 7፣ ሀምሌ 1972)

 

© አፈንዲ ሙተቂ

በላይ ዘለቀ
ከስብሐት ገብረ እግዚአብሔር
(የካቲት መጽሔት፣ 3ኛ ዓመት ቁጥር 7፣ ሀምሌ 1972)

----------------------------------------
ማስታወሻ፡- ከታች እንደምታነቡት ጋሽ ስብሐት በዚህ ጽሁፍ ውስጥ “በላይ ዘለቀ ፎቶ ተነስቶ አያውቅም” የሚል ነገር አስፍሮ ነበር። ይህም የሆነው ታሪኩን ለስብሐት የነገሩት ሰዎች በወቅቱ በላይ ፎቶ መነሳቱን መረጃው ስላልነበራቸው ነው። ይሁንና እዚህ የምትመለከቱት ፎቶ የበላይ ዘለቀ መሆኑ በብዙ ምንጮች ተረጋግጧል። ታዲያ ይህ ፎቶግራፍ በጽሑፉ ውስጥ ስለበላይ ዘለቀ ቁመና ከተነገረው ገለጻ ጋር አንድ ዓይነት መሆኑ በጣም አስደንቆኛል (ጽሑፉ በታተመበት ወቅት የበላይ ቁመና በስዕል ነበር የተገለጸው)።
እኔ ይህንን ጽሁፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት በነሐሴ ወር 1982 ነው። ጸሑፉ የበላይ ዘለቀ እውነተኛ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የወጣበት በመሆኑ ለረጅም ጊዜ ስፈልገው ነበር። በቅርቡ በኢንተርኔት ላይ ተጭኖ ሳገኘው አስደሰተኝና ለናንተ ላካፍላችሁ ወሰንኩ። መልካም ንባብ!
አፈንዲ ሙተቂ
----------------------------------------
ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ የ74 አመት አዛውንት ናቸው ::"እኔና በላይ ዘለቀ የወንድማማች ልጆች ነን "አሉኝ ::"በእድሜ 4 አመት እበልጠዋለሁ ::" እንግዲህ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ይኼን ጊዜ 70 አመታቸው ነበር ማለት ነው :: ፊታውራሪ ተሰማ ላቀው 67 አመታቸው ነው :: "የበላይ ዘለቀ ያባቱ ትንሽ ወንድም ነኝ” አሉኝ :: ፊታውራሪ ቀለመወርቅ መዝጊያ 62 አመታቸው ነው ::የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዋና ጸሀፊ ነበሩ ::የሚከተለውን ታሪክ የነገሩኝ እነዚህ 3 አዛውንቶች ናቸው ::

በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ

ዘለቀ ላቀው (የበላይ ዘለቀ አባት ) የልጅ እያሱ አንጋች ነበሩ ። ልጅ እያሱ ሲገለበጡ ዘለቀ ላቀው ወደ ሚስታቸው አገር ወደ ጫቀታ ሄደው ልጆቻቸውን ይዘው ወደ አገራቸው ወደ ለምጨን (ቢቸና ወረዳ ) ተሻገሩ ። (ቢቸና ጎጃም ውስጥ ጫቀታ ወሎ ውስጥ ከአባይ ወንዝ ማዶ ለማዶ ናቸው ። ይገበያያሉ ፡ ይጋባሉም። )

በ1916 አ.ም. ማለት በላይ ዘለቀ የ14 አመት ልጅ ሳለ ፊታውራሪ እምቢ አለ የተባለ የራስ ሀይሉ ሌባ አዳኝ (ጸጥታ አስከባሪ) ዘለቀ ላቀውን ከበባቸው። ዘለቀ ላቀው እጄን አልሰጥም ስላሉ ተኩስ ተከፈተ። ዘለቀ ላቀውና አብረዋቸው የነበረ አለሙ መርሻ የተባሉ ወንድማቸው ከአስር ሰው በላይ ገድለው ብዙ ሰው አቆሰሉ።

«እኛ ልጆች ተኩስ ካባራ በኋላ ተየጫካው ስንመለስ ሁለቱም ሞተዋል። የዘለቀ ላቀው ሬሳ እቤቱ በራፍ ላይ ተሰቅሎዋል» አሉ ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ ። እንግዲህ በላይ ዘለቀና ተሻለ አለሙ እኩል አባቶቻቸውን አጡ። አብረው የሀዘንን ጽዋ ቀመሱ ፡ እኩል በቀልን እያሰላሰሉ አደጉ ፡ በሁዋላም አብረው ጠላትን ተዋጉ ።
ዘለቀ ላቀው ሲሞቱ ልጆቻቸው ወደ እናታቸው አገር ወደ ጫቀታ ተመለሱ። በላይ ዘለቀ ያባቱን ደም ለመመለስ ተኩስ እየተማረ አደገ። አደገና ያባቱን «ናስ ማሰር» (ባለ ነሐስ ማሰርያ ) ውጅግራ ጠመንጃ ይዞ ወደ አባቱ አገር ወደ ለምጨን (ቢቸና) ተሻገረ ።

አባቶቻቸው የተገደሉባቸው ጎረምሶች ዳኝነት እንዳይሹ ዳኛው ራስ ሀይሉ ሆኑባቸው። የቀራቸው ምርጫ በቀል ነው ።
መሳርያ እየገዙ እየተዘጋጁ ለምጨን ቀንጦ ማርያም እያረሱ ፡ ቀን ይጠብቁ ጀመር።
እንዲህ ሲል ጥልያን መጣ ...በሚያዝያ 28 ቀን (1928 አ.ም.) ለቀኛዝማች መሸሻ ጥልያን መሳርያ በአየር አወረደላቸው። (ለጥልያን ገቡ ) ካለው ሰበካ ያዙ። በረንታ ወረዳ (ቢቸና አውራጃ ) ደረሱ። የዱሀ ከተማ ሰፍረው ህዝቡን መሳርያ እየነጠቁ (ጥልያንን እንዳይወጋ ) ጥልያን ደግ መንግስት ነውና እንገዛለን እያሉ ይሰብካሉ (እንዲሾማቸው)።

«ልጅ በላይ ዘለቀ ግን እዋጋለሁ እንዋጋ እያለ እኛን ወንድሞቹን አነሳሳን» አሉ ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ «ቀሰቀሰን ከሰላሳ እስከ ሀምሳ የምንደርስ ያንድ አያት ልጆች ...የገልገል ቂልጡ ልጆች ...ታጥቀን ተነሳን። ከቀኛዝማች በላይ መሸሻ ሰዎች መሳርያ እየነጠቅን በረሀ ገባን ።»

«ጦር ሲያሳድደን ...ስንሸሽ ...ቤት ሲያቃጥልብን ... ከሁዋላው ወይም ከጎኑ በድንገት እየመታነው መሳርያ ነጥቀን ስናመልጥ .....እንዲህ ስንል አንድ ቀን የማናልፈው ጉዳይ መጣ። ግንባር መግጠም ግድ ሆነ ። ጠላት መሸሻ አሳጣና ።»
«የዛሬን ጦር ማን ይምራው ?» አለን ልጅ በላይ
«አንተን መርጠናል ...እስከ መጨረሻው» አልነው።
"ሁላችሁም ወንድማማች ናችሁ ።" አልኳቸው ፊታውራሪ ተሻለን "በላይ ዘለቀን እርስዎ እንኩዋን በ4 አመት እበልጠዋለሁ ብለዋል ። እንግዲያው በምኑ ነው አለቃችሁ እንዲሆን የመረጣችሁት ?"
"እንዴ ! በደግነቱ ፡ በጀግንነቱ ! ጠባየ መልካም በመሆኑ ! እኔ ይቅርብኝ ብሎ ለሌላው ስለሚያዝን !" (ያን ጊዜ ፡ 1928 አ.ም. ልጅ በላይ 3 ወልደዋል ። ልጅ ተሻለ ግን ገና በታህሳስ ነው ያገቡት)።

ወይዘሮ ድንቅነሽ ሀይሉ (የራስ ሀይሉ ልጅ ) ጥልያን ሾመዋቸው የለምጨን ጉልተ ገዥ ሆነው ሄዱ። ህዝቡን መሳርያ አግባ ብለው አሰባሰቡ። በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ በድንገት ገብተው መሳርያዎቹን ነጥቀው ሴትየዋን ሳይጎዱ ሳያጎሳቁሉ ወደ መጡበት መልሰው ላኩዋቸው ። የነጠቁዋቸውን መሳርያ 35 ያህል ጠመንጃ ዋሻ ደበቁት። ለራሳቸው በቂ መሳርያ ይዘዋላ።
ከዚህ በሁዋላ ደብረ ማርቆስን ጥልያን እየያዘ በላይ ዘለቀን ያሳድነው ጀመር ። ከ1928 አ.ም. ሚያዝያ እስከ ግንቦት 29 ቀን ድረስ ሁኔታው ተመሳሳይና ተደጋጋሚ ነበር። ጦር ይመጣል ...ያስሳል .....እነ በላይ ዘለቀ ይሸሻሉ ...በሁዋላ ቀስ ብለው መጥተው ጥቂቱን ገድለው መሳርያ ነጥቀው ....እልም ! መሳርያ በየዋሸው ያከማቻሉ።
እንደዚህ ብዙ አሰሳ ተሞከረ። ባንዱ አሰሳ የበላይ ዘለቀ ቤትና የለምጨን ቤቶች በሙሉ ተቃጠሉ። ከብቱም ተዘረፈ ። ጠላት ለምጨን 3 ጊዜ ነው ያቃጠለው።

"እስከ ታህሳስ 29 ቀን ድረስ አሰሳው የሚካሄደው በባንዳ ነበር ።" በታህሳስ 8 ቀን 1929 ግብጣን ደበቡ የተባለ ጥልያን ቢቸና ገባ ቢሉን ከዲማ ገስግሰን ቢቸና አደጋ ልንጥል ስንል ካህናት ጽላት ይዘው ስእል መስቀል ይዘው "አገሩንና ታቦቱን ያቃጥልብናልና አትውጉት ። እሱን እኛ ተመለስ እንለዋለን ።" ብለው መለሱን ። ግብጣን ደበቡም በላይ ዘለቀ መጣብህ ቢሉት ወደማርቆስ ተመለሰ ።"

በየካቲት 29 ጥልያን አገሩን አስነስቶ ወረረን ። ከያውራጃው ግብጣን ደበቡ አስከተተ ። ጦር ሲመጣባቸው እነ በላይ ዘለቀ ሸሹ ። አጥቷቸው ሲመለሱ እያደፈጠ በጎን አደጋ እየጣሉ ብዙ መሳርያ ነጠቁት ።
"የግንቦት እርገት ለት ..በ29 ነበር የዋለ ..ጥልያን ራሱ መጣ" የበላይ ዘለቀን ዘመዶች ከለምጨን እየደበደቡ ወደ አርበኞቹ እንዲመሩዋቸው አስገደዱዋቸው ። "ጦሩ ሲመጣ አሳለፍነው ። ከጎን አደጋ ጣልንበት ። በላይ ዘለቀ አንዱን ትሊንቲ ገደለው ኩረኔሉን አቆሰለው ። ብዙ ባንዳዎች ሞቱ ።"

ታስሮ እየተደበደበ ሲመራ የነበረው አዛዥ ቢያዝን ዱብዳ የተባለው የበላይ ዘለቀ ዘመድም ቆሰለ ።
በሰኔ 29 (1929) ጠላት በቅምቧት በደጀን በገበያ በሽበል በበረንታ የነበረውን "ደንበኛ " በሙሉ አከተተው ። (ደንበኛ የሚባለው "የመንግስት " የደንብ ብረት የያዘ ነፍጠኛ ነው ) ቀኛዝማች ስማ ነገዎ አዝማች ሆኖ ይህን ሁሉ አስከትቶ አባይ ወረደና አባራ ጂወርጂስ ሰፈረ ። ሀሳቡ እነ በላይ ዘለቀ ወደ ጫቀታ እንዳይሻገሩ በር በሩን ለመዝጋት ነበር ።
"እንውጋው " አለ በላይ ዘለቀ

"ጦሩ በጣም ብዙ ነው አንችለውም " አሉት ሌሎቹ። "ግድ የለም ።ጦሩ በየመንደሩ ይመራል ። አዝማቹ ላይ አደጋ እንጣልበት ።"
እነ በላይ ዘለቀ ፡ ቀኛዝማች ለማ ነገዎ ያደረበትን በለሊት ከበቡት ። ሲነጋ ለማ ነገኦን ከነወንድሞቹ ደመሰሱት ። ጦሩ በሙሉ እጁን ሰጠ ። መሳሪያውንና በቅሎውን ሁሉ አስረከበ ። ድል አድራጊዎቹ መሳርያውን ዋሻ ውስጥ ደበቁት ። በቅሎዎቹን ወደ ጫቀታ ልከው በጥይት ለወጡዋቸው ።" ይሄ የሆነው ሰኔ 10 ነበር። ሰኔ 12 በአውሮፕላን ይደበድቡን ጀመር ። በረንታ ጎይ ጂወርጂስ ላይ 12 ሰው ሞተብን ። እኛም ተመልሰን ወደ በረሀችን ሸሸን ።" ፊታውራሪ ለማ ሞገስ የጣልያን የጦር እንደራሴ ሆኖ ከማርቆስ ተልኮ ወጥቶ ዲማ አጠገብ ገድ ወንዝ ዋሻ ውስጥ እንዳለ ከበባቸው ። ወጥተው ገጠሙ ። ድል ነሱት ።
ብዙ ሰው ሞተበት ። እሱ ግን አመለጠ ።
በላይ ዘለቀ 60 ያህል ምንሽርና አልቤን ማረከ ። ምንሽርና አልቤን ሲያገኙ የመጀመርያ ጊዜያቸው ነበር ። እስካሁን ግን ሲዋጉ በናስማስር ፡ በውጅግራ ፡ በለበን ብቻ ነበር ።
"ድፍን ሀምሌን ተከበብን ። ለምጨን አንድ ዋሻ ገብተን ተደበቅን ። እኛን ሲያጣን ጊዜ የጎይ ጂወርጂስና ያካባቢውን ህዝብ ጎይ ላይ ሰብስቦ በላይ ዘለቀን ካላመጣችሁ ብሎ በመትረየስ ፈጃቸው ።" በላይ ዘለቀ የቶክሱ እለት ሞቶ ተቀብሯል ተብሎ ለጥልያኖች ተነገራቸው። ሰው ሰደው መቃብሩን ቢያስመረምሩት ሴት ሆና ተገኘች ።
አንዱ አሳባቂ በላይ ዘለቀ ወደ እነብሰ አውራጃ ነው የሄደው ብሎ ለጥልያኖች ጠቆማቸው ። የጥልያን ጦር ወደ እነብሴ ዘመተ። የእነብሴና የጎንቻ ህዝብ ገጠመውና ጨረሰው ። አንድ ጥልያን ብቻ አመለጠ ።

በላይ ዘለቀና አገሬው
እስከ ነሀሴ 1929 ድረስ የበላይ ዘለቀ ተከታዮች ከ30 እስከ 50 የሚደርሱ ወንድሞቹ ብቻ ነበሩ ።
"ነሀሴ ጂወርጂስ በላይ ዘለቀ በረንታ ላይ አዋጅ አስነገረ። እኛን ምሰሉ ፡ እርዱን ። አለዚያ ግን ይህ የጦር ሜዳ ነውና እንዳትጎዱ ሂዱ ልቀቁ።"
"እናርጅ እናውጋ (የደብረወርቅ ወረዳ ) በረንታና ሸበል፡ ጉበያ (ደጀን አጠገብ ) እነማይ (ቢቸና አውራጃ ) ...ይሄ ሁሉ አመነ ፡ ተባበረን።
"ከህዳር ማርያም (1930) እስከ መጋቢት ውድማትን ፡ አዋባልን ፡ ቅምብዋትን ፡ ሊበንን ፡ ባስን ፡ አነድድን ደጀንን ...እነዚህን ያዝን ።"
"በየካቲት ትሊንቲ ከጫቀታ ዘመተብን አባይ ደረሰ ። አገድነው ። ብዙ ውጊያ ተደረገ ። 80 ብረት (ከነሰው ) ማረክን ። መለስነው ። ወደ ደጀን ተመለስን ።"
"ከሸዋ ሲዘምትብን አባይ ላይ አገድነው። ወር ካስራምስት ቀን ተዋጋነው። 3 መኪናዎች ሰበርን ። ውስጣቸው የነበሩ ጥልያኖች ሞቱ ።

"ጥልያን ሀይሉን አጠናክሮ በደጀን በኩል ከሸዋ መጣብን ። 12 በጦለኔ በጀኔራል ማሊን አዝማችነት መጣ ።
"መጋቢት 19 ቀን (1930) ውጊያው ማለዳ የጀመረ በአስራ አንድ ተኩል አበቃ ። መትረየስና መድፍ ከታች ፈረሰኛ በሻምላ (በጎራዴ ) " ተጨምሮበት ከላይ አሮብላ። ወንድሞቻችን አለቁ ። የጦር አዝማች የነበረው የበላይ ዘለቀ ወንድም ደጃዝማች ታደለ ላወቅ ወደቀ ። ተሰማ ላቀው ቆስሎ አመለጠ ። 300 ያህል አለቅን ። የተቀረውን ጨለማ ገላገለን ።
"ጠላት ፆን ማርቆስ ገባ ::እኛ ወደ በረሀችን ገባን ::"
"ሚያዝያ 4 (1930) እበረሀችን አፋፍ ላይ እንደ ሰፈርን ጠላት ባራት ረድፍ ቢቸና ገባ። ሚያዝያ 6 ጦሩን ባራት ማእዘን አቀነባብሮ በረሀችንን በሙሉ ከበበው ። በመካከሉ ደግሞ በግንባር እልፍ አእላፋት ጦር ይዞ ተሰለፈ ።"
"ባለው ሀይላችን ገጠምነው ።"
"ሊያፍነን ሞከረ በብዛቱ ።"
"የቆላ ጫካ ነው ....እሳት ለቀቅንበት "
"ይገርማል እኮ የቀን ነገር !ነፋሱ እሳቱን እያንቦገቦገ ወደነሱ ወሰደው ። ብዙዎቹን እሳት በላቸው ። ብዙዎቹ አመለጡ ። "የበላይ ዘለቀ ሚስት ወይዘሮ ሸክሚቱ አለማየሁ በመትረየስ ሞቱ (እንደ ወንድ ለብሰው ነበር ) ልጅ የሻሸወርቅ በላይ ተማረከች ። የናትየዋ እናትም ተማረከች ። "ከዚህ በሁዋላ አባይን ተሻግረን ጫቀታ ገባን ። ያጌ ከተማ ግዛው ሰብስቤ የተባለው የጥልያን እንደራሴ ገድለን አገሩን አቃጥለን የጎበዝ አለቃ ሾመን ... ፊታውራሪንና ቀኛዝማች እያሱ ልጅ በላይ ሾመው ...ተመልሰን ወደ ለምጨን በረሀ ገባን ።"
© አፈንዲ ሙተቂ

በላይ ዘለቀ
ከስብሐት ገብረ እግዚአብሔር
(የካቲት መጽሔት፣ 3ኛ ዓመት ቁጥር 7፣ ሀምሌ 1972)

—————————————-
ማስታወሻ፡- ከታች እንደምታነቡት ጋሽ ስብሐት በዚህ ጽሁፍ ውስጥ “በላይ ዘለቀ ፎቶ ተነስቶ አያውቅም” የሚል ነገር አስፍሮ ነበር። ይህም የሆነው ታሪኩን ለስብሐት የነገሩት ሰዎች በወቅቱ በላይ ፎቶ መነሳቱን መረጃው ስላልነበራቸው ነው። ይሁንና እዚህ የምትመለከቱት ፎቶ የበላይ ዘለቀ መሆኑ በብዙ ምንጮች ተረጋግጧል። ታዲያ ይህ ፎቶግራፍ በጽሑፉ ውስጥ ስለበላይ ዘለቀ ቁመና ከተነገረው ገለጻ ጋር አንድ ዓይነት መሆኑ በጣም አስደንቆኛል (ጽሑፉ በታተመበት ወቅት የበላይ ቁመና በስዕል ነበር የተገለጸው)።
እኔ ይህንን ጽሁፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያነበብኩት በነሐሴ ወር 1982 ነው። ጸሑፉ የበላይ ዘለቀ እውነተኛ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ይፋ የወጣበት በመሆኑ ለረጅም ጊዜ ስፈልገው ነበር። በቅርቡ በኢንተርኔት ላይ ተጭኖ ሳገኘው አስደሰተኝና ለናንተ ላካፍላችሁ ወሰንኩ። መልካም ንባብ!
አፈንዲ ሙተቂ
—————————————-
ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ የ74 አመት አዛውንት ናቸው ::”እኔና በላይ ዘለቀ የወንድማማች ልጆች ነን “አሉኝ ::”በእድሜ 4 አመት እበልጠዋለሁ ::” እንግዲህ ደጃዝማች በላይ ዘለቀ ይኼን ጊዜ 70 አመታቸው ነበር ማለት ነው :: ፊታውራሪ ተሰማ ላቀው 67 አመታቸው ነው :: “የበላይ ዘለቀ ያባቱ ትንሽ ወንድም ነኝ” አሉኝ :: ፊታውራሪ ቀለመወርቅ መዝጊያ 62 አመታቸው ነው ::የደጃዝማች በላይ ዘለቀ ዋና ጸሀፊ ነበሩ ::የሚከተለውን ታሪክ የነገሩኝ እነዚህ 3 አዛውንቶች ናቸው ::

በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ

ዘለቀ ላቀው (የበላይ ዘለቀ አባት ) የልጅ እያሱ አንጋች ነበሩ ። ልጅ እያሱ ሲገለበጡ ዘለቀ ላቀው ወደ ሚስታቸው አገር ወደ ጫቀታ ሄደው ልጆቻቸውን ይዘው ወደ አገራቸው ወደ ለምጨን (ቢቸና ወረዳ ) ተሻገሩ ። (ቢቸና ጎጃም ውስጥ ጫቀታ ወሎ ውስጥ ከአባይ ወንዝ ማዶ ለማዶ ናቸው ። ይገበያያሉ ፡ ይጋባሉም። )

በ1916 አ.ም. ማለት በላይ ዘለቀ የ14 አመት ልጅ ሳለ ፊታውራሪ እምቢ አለ የተባለ የራስ ሀይሉ ሌባ አዳኝ (ጸጥታ አስከባሪ) ዘለቀ ላቀውን ከበባቸው። ዘለቀ ላቀው እጄን አልሰጥም ስላሉ ተኩስ ተከፈተ። ዘለቀ ላቀውና አብረዋቸው የነበረ አለሙ መርሻ የተባሉ ወንድማቸው ከአስር ሰው በላይ ገድለው ብዙ ሰው አቆሰሉ።

«እኛ ልጆች ተኩስ ካባራ በኋላ ተየጫካው ስንመለስ ሁለቱም ሞተዋል። የዘለቀ ላቀው ሬሳ እቤቱ በራፍ ላይ ተሰቅሎዋል» አሉ ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ ። እንግዲህ በላይ ዘለቀና ተሻለ አለሙ እኩል አባቶቻቸውን አጡ። አብረው የሀዘንን ጽዋ ቀመሱ ፡ እኩል በቀልን እያሰላሰሉ አደጉ ፡ በሁዋላም አብረው ጠላትን ተዋጉ ።
ዘለቀ ላቀው ሲሞቱ ልጆቻቸው ወደ እናታቸው አገር ወደ ጫቀታ ተመለሱ። በላይ ዘለቀ ያባቱን ደም ለመመለስ ተኩስ እየተማረ አደገ። አደገና ያባቱን «ናስ ማሰር» (ባለ ነሐስ ማሰርያ ) ውጅግራ ጠመንጃ ይዞ ወደ አባቱ አገር ወደ ለምጨን (ቢቸና) ተሻገረ ።

አባቶቻቸው የተገደሉባቸው ጎረምሶች ዳኝነት እንዳይሹ ዳኛው ራስ ሀይሉ ሆኑባቸው። የቀራቸው ምርጫ በቀል ነው ።
መሳርያ እየገዙ እየተዘጋጁ ለምጨን ቀንጦ ማርያም እያረሱ ፡ ቀን ይጠብቁ ጀመር።
እንዲህ ሲል ጥልያን መጣ …በሚያዝያ 28 ቀን (1928 አ.ም.) ለቀኛዝማች መሸሻ ጥልያን መሳርያ በአየር አወረደላቸው። (ለጥልያን ገቡ ) ካለው ሰበካ ያዙ። በረንታ ወረዳ (ቢቸና አውራጃ ) ደረሱ። የዱሀ ከተማ ሰፍረው ህዝቡን መሳርያ እየነጠቁ (ጥልያንን እንዳይወጋ ) ጥልያን ደግ መንግስት ነውና እንገዛለን እያሉ ይሰብካሉ (እንዲሾማቸው)።

«ልጅ በላይ ዘለቀ ግን እዋጋለሁ እንዋጋ እያለ እኛን ወንድሞቹን አነሳሳን» አሉ ፊታውራሪ ተሻለ አለሙ «ቀሰቀሰን ከሰላሳ እስከ ሀምሳ የምንደርስ ያንድ አያት ልጆች …የገልገል ቂልጡ ልጆች …ታጥቀን ተነሳን። ከቀኛዝማች በላይ መሸሻ ሰዎች መሳርያ እየነጠቅን በረሀ ገባን ።»

«ጦር ሲያሳድደን …ስንሸሽ …ቤት ሲያቃጥልብን … ከሁዋላው ወይም ከጎኑ በድንገት እየመታነው መሳርያ ነጥቀን ስናመልጥ …..እንዲህ ስንል አንድ ቀን የማናልፈው ጉዳይ መጣ። ግንባር መግጠም ግድ ሆነ ። ጠላት መሸሻ አሳጣና ።»
«የዛሬን ጦር ማን ይምራው ?» አለን ልጅ በላይ
«አንተን መርጠናል …እስከ መጨረሻው» አልነው።
“ሁላችሁም ወንድማማች ናችሁ ።” አልኳቸው ፊታውራሪ ተሻለን “በላይ ዘለቀን እርስዎ እንኩዋን በ4 አመት እበልጠዋለሁ ብለዋል ። እንግዲያው በምኑ ነው አለቃችሁ እንዲሆን የመረጣችሁት ?”
“እንዴ ! በደግነቱ ፡ በጀግንነቱ ! ጠባየ መልካም በመሆኑ ! እኔ ይቅርብኝ ብሎ ለሌላው ስለሚያዝን !” (ያን ጊዜ ፡ 1928 አ.ም. ልጅ በላይ 3 ወልደዋል ። ልጅ ተሻለ ግን ገና በታህሳስ ነው ያገቡት)።

ወይዘሮ ድንቅነሽ ሀይሉ (የራስ ሀይሉ ልጅ ) ጥልያን ሾመዋቸው የለምጨን ጉልተ ገዥ ሆነው ሄዱ። ህዝቡን መሳርያ አግባ ብለው አሰባሰቡ። በላይ ዘለቀና ወንድሞቹ በድንገት ገብተው መሳርያዎቹን ነጥቀው ሴትየዋን ሳይጎዱ ሳያጎሳቁሉ ወደ መጡበት መልሰው ላኩዋቸው ። የነጠቁዋቸውን መሳርያ 35 ያህል ጠመንጃ ዋሻ ደበቁት። ለራሳቸው በቂ መሳርያ ይዘዋላ።
ከዚህ በሁዋላ ደብረ ማርቆስን ጥልያን እየያዘ በላይ ዘለቀን ያሳድነው ጀመር ። ከ1928 አ.ም. ሚያዝያ እስከ ግንቦት 29 ቀን ድረስ ሁኔታው ተመሳሳይና ተደጋጋሚ ነበር። ጦር ይመጣል …ያስሳል …..እነ በላይ ዘለቀ ይሸሻሉ …በሁዋላ ቀስ ብለው መጥተው ጥቂቱን ገድለው መሳርያ ነጥቀው ….እልም ! መሳርያ በየዋሸው ያከማቻሉ።
እንደዚህ ብዙ አሰሳ ተሞከረ። ባንዱ አሰሳ የበላይ ዘለቀ ቤትና የለምጨን ቤቶች በሙሉ ተቃጠሉ። ከብቱም ተዘረፈ ። ጠላት ለምጨን 3 ጊዜ ነው ያቃጠለው።

“እስከ ታህሳስ 29 ቀን ድረስ አሰሳው የሚካሄደው በባንዳ ነበር ።” በታህሳስ 8 ቀን 1929 ግብጣን ደበቡ የተባለ ጥልያን ቢቸና ገባ ቢሉን ከዲማ ገስግሰን ቢቸና አደጋ ልንጥል ስንል ካህናት ጽላት ይዘው ስእል መስቀል ይዘው “አገሩንና ታቦቱን ያቃጥልብናልና አትውጉት ። እሱን እኛ ተመለስ እንለዋለን ።” ብለው መለሱን ። ግብጣን ደበቡም በላይ ዘለቀ መጣብህ ቢሉት ወደማርቆስ ተመለሰ ።”

በየካቲት 29 ጥልያን አገሩን አስነስቶ ወረረን ። ከያውራጃው ግብጣን ደበቡ አስከተተ ። ጦር ሲመጣባቸው እነ በላይ ዘለቀ ሸሹ ። አጥቷቸው ሲመለሱ እያደፈጠ በጎን አደጋ እየጣሉ ብዙ መሳርያ ነጠቁት ።
“የግንቦት እርገት ለት ..በ29 ነበር የዋለ ..ጥልያን ራሱ መጣ” የበላይ ዘለቀን ዘመዶች ከለምጨን እየደበደቡ ወደ አርበኞቹ እንዲመሩዋቸው አስገደዱዋቸው ። “ጦሩ ሲመጣ አሳለፍነው ። ከጎን አደጋ ጣልንበት ። በላይ ዘለቀ አንዱን ትሊንቲ ገደለው ኩረኔሉን አቆሰለው ። ብዙ ባንዳዎች ሞቱ ።”

ታስሮ እየተደበደበ ሲመራ የነበረው አዛዥ ቢያዝን ዱብዳ የተባለው የበላይ ዘለቀ ዘመድም ቆሰለ ።
በሰኔ 29 (1929) ጠላት በቅምቧት በደጀን በገበያ በሽበል በበረንታ የነበረውን “ደንበኛ ” በሙሉ አከተተው ። (ደንበኛ የሚባለው “የመንግስት ” የደንብ ብረት የያዘ ነፍጠኛ ነው ) ቀኛዝማች ስማ ነገዎ አዝማች ሆኖ ይህን ሁሉ አስከትቶ አባይ ወረደና አባራ ጂወርጂስ ሰፈረ ። ሀሳቡ እነ በላይ ዘለቀ ወደ ጫቀታ እንዳይሻገሩ በር በሩን ለመዝጋት ነበር ።
“እንውጋው ” አለ በላይ ዘለቀ

“ጦሩ በጣም ብዙ ነው አንችለውም ” አሉት ሌሎቹ። “ግድ የለም ።ጦሩ በየመንደሩ ይመራል ። አዝማቹ ላይ አደጋ እንጣልበት ።”
እነ በላይ ዘለቀ ፡ ቀኛዝማች ለማ ነገዎ ያደረበትን በለሊት ከበቡት ። ሲነጋ ለማ ነገኦን ከነወንድሞቹ ደመሰሱት ። ጦሩ በሙሉ እጁን ሰጠ ። መሳሪያውንና በቅሎውን ሁሉ አስረከበ ። ድል አድራጊዎቹ መሳርያውን ዋሻ ውስጥ ደበቁት ። በቅሎዎቹን ወደ ጫቀታ ልከው በጥይት ለወጡዋቸው ።” ይሄ የሆነው ሰኔ 10 ነበር። ሰኔ 12 በአውሮፕላን ይደበድቡን ጀመር ። በረንታ ጎይ ጂወርጂስ ላይ 12 ሰው ሞተብን ። እኛም ተመልሰን ወደ በረሀችን ሸሸን ።” ፊታውራሪ ለማ ሞገስ የጣልያን የጦር እንደራሴ ሆኖ ከማርቆስ ተልኮ ወጥቶ ዲማ አጠገብ ገድ ወንዝ ዋሻ ውስጥ እንዳለ ከበባቸው ። ወጥተው ገጠሙ ። ድል ነሱት ።
ብዙ ሰው ሞተበት ። እሱ ግን አመለጠ ።
በላይ ዘለቀ 60 ያህል ምንሽርና አልቤን ማረከ ። ምንሽርና አልቤን ሲያገኙ የመጀመርያ ጊዜያቸው ነበር ። እስካሁን ግን ሲዋጉ በናስማስር ፡ በውጅግራ ፡ በለበን ብቻ ነበር ።
“ድፍን ሀምሌን ተከበብን ። ለምጨን አንድ ዋሻ ገብተን ተደበቅን ። እኛን ሲያጣን ጊዜ የጎይ ጂወርጂስና ያካባቢውን ህዝብ ጎይ ላይ ሰብስቦ በላይ ዘለቀን ካላመጣችሁ ብሎ በመትረየስ ፈጃቸው ።” በላይ ዘለቀ የቶክሱ እለት ሞቶ ተቀብሯል ተብሎ ለጥልያኖች ተነገራቸው። ሰው ሰደው መቃብሩን ቢያስመረምሩት ሴት ሆና ተገኘች ።
አንዱ አሳባቂ በላይ ዘለቀ ወደ እነብሰ አውራጃ ነው የሄደው ብሎ ለጥልያኖች ጠቆማቸው ። የጥልያን ጦር ወደ እነብሴ ዘመተ። የእነብሴና የጎንቻ ህዝብ ገጠመውና ጨረሰው ። አንድ ጥልያን ብቻ አመለጠ ።

በላይ ዘለቀና አገሬው
እስከ ነሀሴ 1929 ድረስ የበላይ ዘለቀ ተከታዮች ከ30 እስከ 50 የሚደርሱ ወንድሞቹ ብቻ ነበሩ ።
“ነሀሴ ጂወርጂስ በላይ ዘለቀ በረንታ ላይ አዋጅ አስነገረ። እኛን ምሰሉ ፡ እርዱን ። አለዚያ ግን ይህ የጦር ሜዳ ነውና እንዳትጎዱ ሂዱ ልቀቁ።”
“እናርጅ እናውጋ (የደብረወርቅ ወረዳ ) በረንታና ሸበል፡ ጉበያ (ደጀን አጠገብ ) እነማይ (ቢቸና አውራጃ ) …ይሄ ሁሉ አመነ ፡ ተባበረን።
“ከህዳር ማርያም (1930) እስከ መጋቢት ውድማትን ፡ አዋባልን ፡ ቅምብዋትን ፡ ሊበንን ፡ ባስን ፡ አነድድን ደጀንን …እነዚህን ያዝን ።”
“በየካቲት ትሊንቲ ከጫቀታ ዘመተብን አባይ ደረሰ ። አገድነው ። ብዙ ውጊያ ተደረገ ። 80 ብረት (ከነሰው ) ማረክን ። መለስነው ። ወደ ደጀን ተመለስን ።”
“ከሸዋ ሲዘምትብን አባይ ላይ አገድነው። ወር ካስራምስት ቀን ተዋጋነው። 3 መኪናዎች ሰበርን ። ውስጣቸው የነበሩ ጥልያኖች ሞቱ ።

“ጥልያን ሀይሉን አጠናክሮ በደጀን በኩል ከሸዋ መጣብን ። 12 በጦለኔ በጀኔራል ማሊን አዝማችነት መጣ ።
“መጋቢት 19 ቀን (1930) ውጊያው ማለዳ የጀመረ በአስራ አንድ ተኩል አበቃ ። መትረየስና መድፍ ከታች ፈረሰኛ በሻምላ (በጎራዴ ) ” ተጨምሮበት ከላይ አሮብላ። ወንድሞቻችን አለቁ ። የጦር አዝማች የነበረው የበላይ ዘለቀ ወንድም ደጃዝማች ታደለ ላወቅ ወደቀ ። ተሰማ ላቀው ቆስሎ አመለጠ ። 300 ያህል አለቅን ። የተቀረውን ጨለማ ገላገለን ።
“ጠላት ፆን ማርቆስ ገባ ::እኛ ወደ በረሀችን ገባን ::”
“ሚያዝያ 4 (1930) እበረሀችን አፋፍ ላይ እንደ ሰፈርን ጠላት ባራት ረድፍ ቢቸና ገባ። ሚያዝያ 6 ጦሩን ባራት ማእዘን አቀነባብሮ በረሀችንን በሙሉ ከበበው ። በመካከሉ ደግሞ በግንባር እልፍ አእላፋት ጦር ይዞ ተሰለፈ ።”
“ባለው ሀይላችን ገጠምነው ።”
“ሊያፍነን ሞከረ በብዛቱ ።”
“የቆላ ጫካ ነው ….እሳት ለቀቅንበት ”
“ይገርማል እኮ የቀን ነገር !ነፋሱ እሳቱን እያንቦገቦገ ወደነሱ ወሰደው ። ብዙዎቹን እሳት በላቸው ። ብዙዎቹ አመለጡ ። “የበላይ ዘለቀ ሚስት ወይዘሮ ሸክሚቱ አለማየሁ በመትረየስ ሞቱ (እንደ ወንድ ለብሰው ነበር ) ልጅ የሻሸወርቅ በላይ ተማረከች ። የናትየዋ እናትም ተማረከች ። “ከዚህ በሁዋላ አባይን ተሻግረን ጫቀታ ገባን ። ያጌ ከተማ ግዛው ሰብስቤ የተባለው የጥልያን እንደራሴ ገድለን አገሩን አቃጥለን የጎበዝ አለቃ ሾመን … ፊታውራሪንና ቀኛዝማች እያሱ ልጅ በላይ ሾመው …ተመልሰን ወደ ለምጨን በረሀ ገባን ።”

በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ዙሪያ የቴሌኮንፍረንስ ጥሪ ለመላው ኢትዮጵያውያን

ሸንጎ በኢትዮ-ሱዳን ድንበር ዙሪያ ሕዝባዊ ውይይትና ገለጻ ለማድረግ የፊታችን እሁድ ፌብሩዋሪ 9 ቀን 2014 ቴሌኮንፈርንስ ጠርቶ ማንኛውም ስለድንበሩ ያገባኛል የሚል ኢትዮጵያዊ እንዲገኝ ጥሪውን አቅርቧል። የጥሪው ወረቀት የሚከተለው ነው፦

የጎንደር ከተማ የጎብኝዎች ካርታ ተዘጋጀ

Thursday, 06 February 2014

የጎንደር ከተማ የጎብኝዎች ካርታው ለጎብኝዎች የተሟላ መረጃ ለማቅረብና የጎብኝዎችን ቁጥር ለማሳደግ እንደሚያግዝ የባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር አስታወቋል፡፡

በጎንደር ከተማ የሚገኙ መስህቦችንና በዙሪያዋ ያሉ የመስህብ ስፍራዎችን የሚመለከት ሙሉ መረጃ የሚሰጥ የጎብኝዎች ካርታ በስፔን መንግስትና በጎንደር ከተማ አስተዳደር ትብብር ተዘጋጅቶ ይፋ ሆኗል፡፡

የጎንደር ከተማን የጎበኝዎች ካርታ በዋናነት ያዘጋጁት ፕሮፌሰር ኤድዋርደ ማርቲን በክልሉ የሚገኙ የመስህብ ስፍራዎችን የሚገልጽ ካርታ ለመስራት ያሰበው የቅርስ ጥናት ስራውን በጎንደር ሲያካሂድ እንደነበር ገልጿል፡፡

‹‹ የጎንደርን የጎብኝዎች ካርታ ለመስራት ያስብኩት የቅርስ ጥናት ስራ እየሰራሁ በነበረበት ጊዜ ነው፡፡ ሁሉንም ታሪካዊ ቦታዎችና የአማራ ክልልን የተፈጥሮና የታሪክ ስብጥር ለመለካት እነዚህን መረጃዎች ለጎብኝዎች በሚሰጥ ካርታ ቢዘጋጅ ጥሩ እንደሆነ አሰብኩ፡፡ ሁሉንም መረጃዎች በተመሳሳይ ይዘት እና ካርታ ላይ ለጎብኝዎች ለማካተትም ቻልኩ፡፡››

የባህልና ቱሪዝም ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ ታደለች ዳሌቾ  የተዘጋጀው ካርታ ታሪካዊ ስፍራዎችን ለሚጎበኙ ሰዎች ሙሉ መረጃ ከመስጠት ባለፈ የጎብኚዎችን ቁጥር ለማሳደግና የጊዜ ቆይታ ለማራዘም ያግዛል ብለዋል፡፡

በ27 ሺህ ዩሮ የተዘጋጀው የጎንደር ከተማ የጎብኝዎች ካርታ በናሽናል ጅኦግራፊ ተቀባይነት አግኝቷል፡፡

የጎንደር ከተማ እንደ በጎርጎሮሳውያኑ ዘመን ቀመር በ1979 በአለም የቅርስ መዝገብ የታሪካዊ ቅርሶች መገኛ በሚል መመዝገቡ ይታወሳል፡፡

ሪፖርተር፡-የልቤ ማዘንጊያ

Source.ertagov.com

Astounding Revelations on the Road to Gondar, Ethiopia the Garden of Eden

02/03/2014

By Bernard Anderson, MD

It was April, 2008, a bleak 5 A.M. in Meskel Square, Addis Ababa that we set out for Gondar, 740 kilometers away on the Sky Bus. It was my third time to make the trip, and I was no longer glued to the vistas on the other side of the window as the bus speedily but steadily made its way through the mountains and villages of the Ethiopian northern highlands. I soon fell asleep, hypnotized by the cold and dark of an Ethiopian morning 2,200 meters above sea level, as well as by the rolling neon sign in big red characters above the driver’s head declaring to all: “Young Entrepreneur, German Engineering, Chinese Price…Young Entrepreneur, German Engineering, Chinese…”.

Road to GondarFirst stop at Dejen marked a successful passage through “The Gorge”- a deep valley cut by the Ghion of the bible, or the Abbay of the Ethiopians, themselves the children of Kis (later the Cush/Kush of the Hebrew), recorded first in the hieroglyphs of Kmt in 1970 BCE.There we got a chance to stretch our legs, use the bathroom and to have lunch in any of several small hotels. All aboard again, we set off to Gondar passing through the towns of Debre Markos, Dembecha, Finote Selam, Injibara, Dangla and finally Bahirdar, at the southern point of lake Tana, (Ethiopia’s largest lake and Africa’s 2nd largest), from where it pours it’s waters into the head of the Abbay to become the Blue Nile in the Sudan.

In Sudan it joins the White Nile at Khartoum, from where it runs for 200 hundred miles north to the city of Saba (Merowe since about 500 BCE), This Saba, was a place where many Ethiopian kings and queens ruled from. There at Saba/Merowe the Nile is joined by the fabled Atbara, “From there the Nile runs for 1700 more miles to the Mediterranean sea as the longest river on the planet Earth giving the gifts of life, high culture, and civilization from the Anu, or the Anu/Agu. The first gifts were to Kmt, meaning Black Land. Kmt, later named Egypt by the Greeks, passed them on to the world. Yes, this same Kmt made us know Osiris, Thoth, Isis, Horus and Maat; gave us Imhotep, the architect of Sacara’s Step Pyramid in 2,700 BCE and according to Breasted, was the author of the Smith papyrus. This African Imhotep, was deified posthumously as God of Medicine 2000 years before Hippocrates swore in his “Oath” to him in the name of Asclepius; the same Kmt gave us the city Akhetaten that made us know one God, the primary creative force of nature, whose emblem was the solar disc and also gave us Moses, who tamed the Apiru/Habiru, gave them the law and even the name of their God Jehovah. This generous Kmt, also gave the world the art of writing. These are just a few of the gifts of Kmt and the Nile, the child of Tana and Atbara. How sad now to see Kmt embroiled in conflict and totally disconnected from its glorious and special past. Read More Bernard-Anderson-MD-Road to Gondar

የአማራ ክልል ም/ ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን የስድብ ውርጅብኝ

 

የአማራ ክልል ም/ ፕሬዚዳንት እና የብአዴን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ አለምነው መኮንን “የአማራው ህዝብ ሰንፋጭ የሆነ ትምክተኝነት የተጠናወተው በመሆኑ በቤንሻንጉልና በሌሎችም ቦታዎች ለመሰደዱ ምክንያት ሆኖታል” በማለት፣ ለብአዴን ነባርና አዳዲስ ካድሬዎች ተናግረዋል።

ካድሬዎቹ “የአማራው ህዝብ ለምን ይሰደዳል? ለምን በእየክልሉ ጥቃት ይደርስበታል? አማራውን ከጥቃት ለመከላከል ለምን ሙከራ አይደረግም በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ሲሆን፣ ም/ል ፕሬዚዳንቱ የአማራው ህዝብ በቅድሚያ እንዳይሰደድ ለማድረግ ስራ እየተሰራ ነው፣ ነገር ግን ከተሰደደ በሁዋላም ቢሆንም ሰንፋጭ የሆነውን ትምክህተኝነቱን በመተው ከሌላው ጋር ለመኖር መልመድ አለበት ብለዋል።

አማራው “በባዶ እግሩ እየሄደ የሚናገረው ንግግር ግን መርዝ ነው” ያሉት ምክትል አስተዳዳሪውና የብአዴን የጽህፈት ቤት ሃላፊው፣ ይሄ መርዝ ንግግሩ አንድ የሚያደርግ አይደለም ሲሉ አክለዋል።
ከኢትዮጵያውያን ጋር አብሮ ለመኖር አማራው የትምክህት ለሃጩን ማራገፍ አለበት ያሉት አቶ አለምነው፣ ይሄ ለሃጭ ሳይራገፍ በጋራ መኖር አይቻልም ሲሉ ድምድመዋል።
ማንኛውም ስም ያወጣ ሙትቻ ፓርቲ ሁሉ መንገሻው አማራ ክልል ነው ያሉት ምክትል ፕሬዚዳንቱ፣ ምክንያቱንም ሲገልጹ ትምክህትን እንደ ምግብ ስለሚመገበው ነው ብለዋል። ያንን ምግብ እየተመገበ እንደሚያቅራራም ገልጸዋል።

እሳትን ያድምጡ