ሁለቱ የጠፉ ‹ጎንደሬዎች›

By Rieye Hulentena
ሁለቱ የጠፉ ‹ጎንደሬዎች›
አዜብ መስፍን/ጎላ/እና እነዬ ታከለ

image

ጎንደር በአስተዳደር፣ በልማት፣ በሥነ- ጥበብ፣ በሥነ- ሕንፃ፣ በማኅበራዊ ሕይወት፣ በለውጥ ግስጋሴ፣…ወዘተ. በኢትዮጵያ ታሪክ ከፍተኛ ሚና ማበርከቷና እያበረከተች እንደምትገኝ ይታወቃል፡፡
ይሁንና እንዳንድ ከአብራኳ የወጡ ክፋዮቿ እያወቁም ሆነ ሳያውቁ ወይም በመታለል የታሪኳን ድባብ ጠለሸት ሲቀቡት ይስተዋላሉ፡፡
በጎንደር ክ/ ሀገር በወገራ አውራጃ በወልቃይት ወረዳ ተወልዳ ለተሀት/ህወሀት የጥፋት ‹ተልእኮ› መረብ ውስጥ የገባችው አዜብ የዳባትን ምግብና ውሃ ጠጥቶ ላደገው የጥፋት መዘውር ለሆነው ክንፈ ገ/ መድኅን በፆታ ጓደኛ በመሆን ህወሃት ላቀደው የወልቃይትና የጠገዴ እንዲሁም የሰቲት ሁመራንና በየዳ ወረራ ከሀዲዋ አዜብ ዋና ተጠማጅ ሆነችላቸው፡፡ በዚህም እንቅፋት ይሆናሉ የተባሉ ጣሪክ አዋቂ አዛውንቶችን፣ ጀግና ተዋጊዎችን፣ ወጣት ዜጎችን፣…ወዘተ. በአዜብ ጠቋሚነት ሲያስሩ፣ ሲያንገላቱ፣ ሲደበድቡ፣ ሲገድሉ፣ ግፍ ሲፈፅሙ፣…ቆዩ፡፡
ያኔ የወለወቃይትና የጠቀደ፣ የበየዳ የጃናሞራ፣ የደባርቅ፣…ጀግኖች በተዋጊነት፣ በሽምቅነት፣ በጀግንነት ከፍተኛ የመመከትና የማሸነፍ ሚና ከመጫጫቻም በላይ የቀሪው ጎንደርና የኢትዮጵያ ክፍል አለመተባበሩ እጅግ አሳዝኗቸዋል፡፡
በዚህም በምእራባውያን ድጋፍና እገዛ የወያኔና የሻዕቢያ ሂደት እየሰፋ ሲመጣ የአዜብ ጉዳይ ለአጥፍቶ ጠፊው መለስ ዜናዊ ተሸጋገረ፡፡ በህወሃት ‹ትግል› ማንም በፆታ ጓደኝነት ቢገኝ ርምጃ ይወሰድበታል፡፡ ነገር ግን የአዜብ ለክንፈና ለመለስ መጎዳኘት ተልእኮ ስለነበረው በ‹ህግ› ጣሽነት አይነሳም፡፡ በዚህም የርሷ የአጥፊነት ሚና በከፍተኛ ሁኔታ ጨመረ፡፡ ከጎንደርነት ባሕል፣ ወግ፣ ልማድ፣ አነጋገር፣ …ጭልጥ ብላ ወጥታ በ‹ትግራዊንት› ተሰለፈች፡፡ እጅግ ዘግናኝ በሆነ ሁኔታም ‹ወገኖቿን› አሰፈጀች፡፡ ሌላው ቀርቶ ዘመዶቿና የትውልድ ቀየዋ ሰዎች በአምባሳደር ዳኘው ወ/ ሥላሴ አቅራቢነት የደረሰባቸውን በደልና ቅሬታ ለመለስ ዜናዊ ሊያቀርቡ ቢሹ ከበር መልስ ‹እኔና መሌ በርሃ ሳለን ማኒፌስቶውን ያፀደቅነው ስለሆነ አታስቸግሩት እርሱ ስራ አከበት አታስፈቱት…› በሚል ውረፋ መልሳቸዋለች፡፡ በቅርቡም በወልቃይት የነፃነት ጉዳይ ሲማገቱ ከነበሩ ወጣቶች አፍነው በማምጣት በማእከላዊ እጅግ ዘግናኝ ድብደባ ፈድረሰውባቸው በቦሌ ሚካኤል አጠገብ ‹የአልሸባብ አጥፍቶ ጠፊዎች ቦምብ በማፈንዳት ፈጸሙ…› በሚል በግፍ እንደገደሏቸው ግልፅ ነው፡፡
በጣም የሚገርመው ‹ሴትዮዋ› ለአስካደ ባላቸው ያላቸው ነገር ነው፡፡ ባሌ ‹የቀድሞ ጠ/ ሚኒስቴር› ተብሎ እይጠራ› ‹ ታላቁ መሪ መለስ ዜናዊ› ተብሎ ይጠራ› ሲሉ ድንፋታ ቢጤ አሰምተዋል፡፡
ወይዘሮ አዜብ መለስ እኮ ላይመለስ በአስከፊ መቅሰፍት ጠፍቷል፡፡ የሀገራችን ታሪክ፣ ፖለቲካ፣ ባሕል፣ አኗኗር፣ ማኅበራዊ ሕይወት፣ ኢኮኖሚ፣ ፍቅር፣ መተባበር፣ አንድነት፣….ምስቅልቅሉን ከማውጣቱ በተጨማሪ ለከፋ ችግር ዳርጎን እኮ ነው ላይመለስ የጠፋው፡፡ መለስ እኮ ከሰይጣንም በላይ የሰው ስጋ የለበሰ ጋኔን ነው፡፡ ‹ታላቅነቱ› ለምንድን ነው? ለክህደት?፣ ለጥፋት?፣ ለውንብድና?፣ ለስርቆት?፣ ለኢሰብአዊነት?፣….ከሆነ እንስማማለን፡፡ ታዲያ ግብሩም አብሮ ከ‹ትልቅነቱ› ጋር ይጠራ፡፡ ታላቁ የክህደት/የውንብድና/ የዘረፋ/ የግፈኞች/ የጨፍጫፊዎች/… መሪ መለስ ዜናዊ ተብሎ በአገባቡ ይጠራ፡፡
ሌላኛዋ ጠፊ ቀደም ሲል የፋሲለደስ የኪነት ቡድን ፈርጥ፣ የሕዝብ ለሕዝብ የባሕል አምባሳደሯ፣ መልከ መልካሟ እነዬ ታከለ ናት፡፡ በጎንደር ክ/ ሀገር ከቆላድባ ምድር ወጥታ የነበራትን የማንነቷን መገለጫ ባሕል፣ ወግ፣ አነጋገር፣ ልማድ፣ ባሕል፣ ወጥታ በ‹ትግሬነት› የተሰለፈችው፡፡
‹እነዬ› በሙያዋ እያገለገለች እያለ የወያኔ ወራሪ ቡድን ወደ ስልጣን የተቆናጠጠበት የደርግ መንግስት የበነነበት ወቅት ስለነበር ህወሃት በልዩ ልዩ መንገድ ለጠፋት ካሰለፋቸው ውስጥ አብርሃ ገ/ መስቀል የጠሰጠውን ተልእኮ ይዞ ቀደም ደርግ ሲያሰራው የነበረውን የሀገር የማስተዋወቅ እንቅስቃሴ ለማደብዘዝ ‹በራሱ መልካም ስሜት እንደሚፈፅም› የፋሲለደስን የኪነት ቡድን ተረክቦ በሰ/ አሜሪካ በመዘዋወር አንዳንድ እንቅሴቃሴዎችን ሲደርግ በደረሰበት ኪሳራ ‹እነዬን› በእቅፉ በማድረግ የነበራትን የባሕል ብርሃን ፈንጣቂነት አስጠፍቶ፣ ከጓደኞቿ በመነጠል ለኢላማው ተጠቀመባት፡፡
‹ዛሬ ላይ በባእድ ሀገር ሰው አልባ ሁኘ የኖርኩት› እያለች የምትነፈርቀው ጠላቷ ማን እንደነበር አልተከሰተላትም፡፡ ‹ጋሸ› የምትለው አጥማጇ መሆኑ፡፡
ለሁሉም የጠፉ ጎንደሬዎች እነዚህን አነሳን እንጂ በጀብደኛነት፣ በጅልነት፣ በድንቁርና፣….ለወንበዴዎች ሎሌ በመሆን በሀገርና በወገን ላይ ውድመት ያደረሱ አያሌዎች ናቸው፡፡ ህወሃት የትግራይ ቁጥር እንዲጨምርና የሌላው ብሔር እንዲዳከም በሀገሪቱ ገንዘብ ውድ ሴቶችን እያማለሉ በየክልሉ ቀለበት በማሰር፣ በመዳር፣ በጓደኝነት በመያዝ ለበርካታ ሴቶች ባል አልባ ልጆችን በማስታቀፍ ቅስማቸውን የሰበሩት ብዙዎችን ነው፡፡
መሠረታችን አንናድ!!!
ራሳችንን እንወቅ! እንጠበቅ!
በንዋይ አንዋልል!!!
ርእይ
አዲስ አበባ- ኢትዮጵያ
20/12/ 2007 ዓ. ም

%d bloggers like this: