ሕዝባዊ እምቢተኝነት፣ ለውጥ እና ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን-(ከኤፍሬም እሸቴ)

Adebabay  (ከኤፍሬም እሸቴ)

ኢትዮጵያ የለውጥ ማዕበል ውስጥ ናት። በመላው አገሪቱ የተቀሰቀሰው እምቢተኝነት በመንግሥት በኩል የገጠመው ጠንካራ እጅ ብዙ ዜጎችን ለሞት፣ ለእስር፣ ለስደት እና ለንብረት ውድመት የዳረገ ሆኗል። በመሆንም ላይ ይገኛል። ይሁን እንጂ የመንግሥት የብረት ጡጫ (አይረን ፊስት) ነገሮችን ከማረጋጋት ውጪ የበለጠ ቀውሱን እያሰፋውና እያበረከተው በመሔድ ላይ ይገኛል። በመንግሥት የሚፈጸሙት መንግሥታዊ ሽብሮች ደግሞ እንደ ቀድሞው ዘመን ተደብቀው የሚቀሩ ሳይሆን በተለያዩ ዘዴዎች ለሕዝብ ዓይንና ጆሮ የሚደርሱ ሆነዋል። በአልሞ ተኳሾች የተገደሉ ወጣቶች፣ በፖሊሶች ድብደባ ሲፈፀም የሚያሳዩ አሰቃቂ ቪዲዮዎች፣ ቃለ ምልልሶች እና የተቃጠሉ ንብረቶች ዘመኑ በፈቀዳቸው ቴክኖሎጂዎች በመሰነድ ላይ ይገኛሉ። ሌላው ቀርቶ መንግሥት ራሱ በምስጢር የሚያደርጋቸው ስብሰባዎች የድምጽ ቅጂዎች የአደባባይ ሲሳይ በመሆን ላይ ናቸው። በዚህ ዘመን ተወርቶና ተፈጽሞ ተደብቆ የሚቀር ምንም ምሥጢር ምንም ወንጀል አይኖርም።

የለውጡ ማዕበል አንዴም ለብ፣ አንዴም ሞቅ፣ አንዴም በረድ እያለ የከረመ ሲሆን አሁን ግን በተለይም በኮንሶ፣ በኦሮሚያ እና በአማራ አያያዙን በማጠናከሩ ወደኋላ ከማይመለስበት ደረጃ ላይ የደረሰ ይመስላል። በአገር ውስጥ ብቻ የሚከናወነው ተቃውሞ አድማሱን በማስፋት በመላው ዓለም ያሉ ኢትዮጵያውያንን እና ትውልደ ኢትዮጵያውያንን በስፋት በማጠቃለል ላይ ነው። በዚያውም መጠን የመንግሥትም ጭካኔ የተሞላበት ርምጃ በከፋ መልኩ ቀጥሏል። መንግሥት በሚያደርገው ሰፊ እንቅስቃሴ ተቃውሞው በተለይ የምዕራባውያን ድጋፍ ሳያገኝ ለመቆየት የቻለ ቢሆንም አትሌት ፈይሳ ሌሊሳ በሪዮ ተቃውሞውን ለዓለም ከገለጠ በኋላ ምዕራባውያንም የሚያውቁትን፣ ነገር ግን ጀርባቸውን የሰጡትን ቀውስ በይፋ ወደመቃወም መግባታቸው እየታየ ነው። ይህ ጽሑፍ በሚዘጋጅበት ወቅት እንኳን የአሜሪካ ኮንግረስ ጉዳዩን ወደ ሕግ ደረጃ ለማድረስ ረቂቅ መዘጋጀቱን ጉዳዩን የሚመሩት የኒውጄርሲ ኮንግረስማን ክሪስ ስሚዝ (Chris Smith) ገልጸዋል።

http://amharic.voanews.com/a/usa-congressman-chris-smith-on-ethiopian-human-right/3505870.html?nocache=1

የቀውሱ መጠን ከአገር አልፎ ዓለም አቀፍ ትኩረት ባገኘበት በአሁኑ ወቅት እኛ ኢትዮጵያውያንን ብቻ ሳይሆን የኢሕአዴግ አጋር የሆኑትን ምዕራባየውያንንም ሳይቀር የሚያሳስባቸው «ቀውሱ በምን መልክ ይጠናቀቃል?» የሚለው ጉዳይ ነው። ይህንን የሚገነዘበው ሕወሐት ዜጋውንም ፈረንጆቹንም ለማስደንበር «የሶሪያ»ን ካርድ በመሳብ ላይ ይገኛል። ተቃውሞው ከቀጠለ እንደ ሶሪያ የጦርና የውድመት አውድማ እንሆናለን በማለት ላይ ነው። ሽማግሌዎቹ መሪዎቹ ከጡረታቸው በመሰባሰብ ይህንኑ «የሶሪያ ካርድ»፣ የጀርመኖችን ሆሎኮስት እና የሩዋንዳን ፍጅት በማንሣት ላይ ናቸው። የኮሙኒኬሽን ዋና መሥሪያ ቤቱ በፎቶዎች የታጀበ የሶሪያ ውድመትን እንደ እያሰራጩ ነው። ጥያቄው ግን በአገራችን ያለው ሕዝባዊ እምቢተኝነት እንጂ ጦርነት አይደለም። አገሪቱን ሶሪያ የሚያደርጋት አውዳሚ ጦር መሣሪያ የያዘው ሕወሐት እና ወታደሩ ነው። ስለዚህ ማስፈራሪያቸውን «እንደ ሶሪያ እናደርጋችኋለን» በሚል እንወስደው ካልሆነ ሌላ ምንም አንድምታ የለውም። የፖለቲካ ምሁራን የራሳቸውን ትንታኔ መስጠታቸው እንደተጠበቀ ሆኖ በበኩላችን «ቀውሱ በምን መልክ ይጠናቀቃል?» የሚለውን በተለይም ከኦርቶዶክሰ ቤተ ክርስቲያን አንጻር ለመመልከት እንሞክራለን።

ሑነት  (Scenario ሴናሪዮ) አንድ፡-

ምንም ለውጥ ሳይመጣ «ዘሀሎ»ው (Status Quo) ከቀጠለ

(ማሳሰቢያ – ዘሀሎ የሚለው ስታትስኩዎ/ Status Quo የሚለውን ቃል የሚተረጉም ነው።)

ሑነት አንድ ለረዥም ጊዜ የቀጠለው ሕዝባዊ እምቢተኝነት በመንግሥት አሸናፊነት ቢደመደም የሚለውን መላምት የተከተለ ነው። ይህ ሑነት ድኅረ 1997 ዓ.ም ምርጫ ያለውን ሑነት ይመስላል። እምቢተኝነቱ በሕዝቡ የበላይነት የማይጠናቀቅ ከሆነ ሕወሐት መራሹ መንግሥት ከ1997 በኋላ እንዳደረገው የዚህ ሕዝባዊ እምቢተኝነት መሪ ናቸው ብሎ የጠረጠራቸው ላይ በሙሉ የማያዳግም ርምጃ ይወስዳል። ይህም በተለይ የራሱ የኢሕአዴግ ክንፎች በሆኑት በብአዴን እና በኦሕዴድ የበታች አመራሮች፣ አባላትና ካዴሬዎቹ ላይ የከረረ ይሆናል። ከዚያም አልፎ ለእምቢተኝነቱ መፈጠር ምቹ ሁኔታ ናቸው የሚባሉትን ነገሮች በሙሉ ያጸዳል። ወጣት መሆን እንደ ወንጀል የሚታይበትን ክፉ አመለካከት ያበረታዋል። ወጣቶች የችግሩ ቀዳሚ ተጠቂዎች መሆናቸው ይቀጥላል። የአገዛዙ ቀንበር ከመቼም ጊዜ በላይ የጠነከረ ይሆናል። የአገዛዙ አካሎች የበለጠ በራስ መተማመን፣ ትዕቢትና ማን አለብኝነት ያሳያሉ። ማንም አያሸንፈንም የሚለው የቆየ ዘፈን የበለጠ ይጠነክራል።

አሁን ያለው ዘሀሎ በዚሁ እንዲቀጥል ትልቅ ፍላጎት ያለው የቤተ ክህነት አመራር የተቆጣጠረው አስተዳደር ያለ እንደመሆኑ ጉዳዩ በሕወሐት/ኢሕአዴግ የበላይነት መጠናቀቁ ለቤተ ክህነቱ መሪዎች ትልቅ እፎይታ እንደሚሆን ይታወቃል። ለዚህም በአቅማቸው የለፉበት እና የሠሩበት፤ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያንን ሙሉ በሙሉ ሽባ በማድረግ የዚህ መንግሥት አገልጋይ ያደረጉ እንደመሆናቸው ሑነት አንድ የልፋታቸው ውጤት ተድርጎ ሊታሰብላቸው ይቻላል።

ይሁን እንጂ ቤተ ክህነቱ ለመንግሥት ባሳየው ጠንካራ ድጋፍ ምክንያት ብዙው ክርስቲያን በመንፈሳዊ ሕይወቱ ረገድ የሚኖረው ቀቢጸ ተስፋ ወትሮም ከነበረው የባሰ መሆኑ አያጠያይቅም። በካህናት እና በመነኮሳት ላይ እንዲሁም በጳጳሳት ላይ የሚኖረው አሉታዊ አመለካከት የበለጠ ስር ይሰድዳል። በምዕራቡ ዓለም በካቶሊክ ካህናት ላይ አሉታዊ አመለካከቶች በመፈጠራቸው ካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን ትልቅ ችግር እንደገጠማት ሁሉ በአገራችንም ቤተ ክርስቲያናችን የዚያ ዕጣ ሊወድቅባት ይችላል። ስለዚህም ከእምነት የሚያፈገፍጉ ሰዎች ቁጥር ሊጨምር ቢችል የሚደንቅ አይሆንም።

በሌላም በኩል የኢሕአዴግ ማሸነፍ እና የበላይነቱን መጨበጥ በተለይም በካህናቱ አካባቢ ያለውን አድርባይነት እና ለፖለቲካው ተገዢ የመሆን «መለካዊ» ኑፋቄ የበለጠ ያሰፋዋል። ቤተ ክርስቲያን ለጣለችባቸው ሃይማኖታዊ ዓላማ ከመቆም ይልቅ በአድርባይነት እና ተመሳስሎ በመኖር አባዜ የፖለቲካውን ከበሮ በመደለቅ የተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያንን የወንጌል ዓላማ የሚዘነጉት ሰዎች ቁጥር አሁን ካለው የበለጠ አሳፋሪ ሆኖ ይቀጥላል። ሙስናው፣ ዓለማዊነቱ፣ አሰረ ክህነትን ያልጠበቁና ምንጫቸው ያልታወቀ መነኮሳት መብዛት፣ ገዳማትና አድባራት እንዲሁም አብነት ት/ቤቶችን መዘንጋቱ የበለጠ እየጨመረ ይሄዳል። ለዚህ መለካዊ ዓላማቸው እንቅፋት ናቸው ብለው የሚያስቧቸውን ተቋማት፣ አገልጋዮች እና አሠራሮች ወደ ማጥፋት ይሄዳሉ።

ሑነት  (Scenario) ቁጥር ሁለት

ጥገናዊ ለውጥ

ሁለተኛውና ይሆናል ተብሎ የሚጠበቀው አንዱ ሑነት መንግሥት «ጥገናዊ ለውጥ በማድረግ ሕዝባዊ እምቢተኝነቱን ያቀዘቅዘዋል» የሚለው መላ ምት ነው። ጥገናዊ ለውጥ መሠረታዊ ለውጥ አይደለም። መንግሥት የያዘውን መሠረታዊ ማንነት ሳይለውጥ አንዳንድ ለውጦችን በማድረግ ከምዕራባውያን አጋሮቹ እና ፖለቲካዊ ብስለት ከጎደላቸው ወገኖች ያጣውን መተማመኛ ማግኘት ነው። የኦሮሞን ጥያቄ ለመመለስ የአዲስ አበባን ማስተር ፕላን ሰርዣለኹ እንዳለውና ጥቂት የሙስሊም መሪዎችን እንደፈታው ያለ የታይታ ምልክቶችን ማድረግ ነው። ነገር ግን እነዚህ ከላይ የተጠቀሱት ርምጃዎች ከማንም አንጀት ጠብ የማይሉ በመሆናቸው ጥገናዊ ለውጥ ውስጥ ሊገቡ የሚችሉ አይደሉም።

ስለዚህ ፈረንጆቹንም፣ አንዳንድ የሕዝባዊ እምቢተኝነቱ ተሳታፊዎችን ቀልብ ሊስብ የሚችለው ጋዜጠኞችን እና የፖለቲካ እስረኞችን መፍታት፣ ቢያንስ ከ1997 ዓ.ም በፊት ወደነበረው ሁኔታ መመለስ ሊሆን ይችላል። ይህ ማለት ሕወሐት በኢህአዴግ ውስጥ ያለውን ድርሻ ሳያስነካ፣ በኢኮኖሚው፣ በውትድርናውና በደኅንነቱ እንዲሁም በሌሎች መንግሥታዊ እርከኖች ላይ ያለውን የአንበሳ ድርሻ ሳያስወስድ በፖለቲካ ፓርቲዎች ላይ የጣለውን የብረት መጋረጃ በጥቂቱ ገለጥ ማድረግ፣ የግል ቴሌቪዥንና ሬዲዮኖችን እንዲሁም ጋዜጣና መጽሔቶችን መፍቀድ፣ ኢሕአዴግ ያልሆኑ ሰዎችን በሥልጣን ላይ ማስቀመጥ የመሳሰሉትን ሊያደርግ ይችላል። በሃይማኖቱ በኩልም አሁን በሥልጣን ላይ ያሉትን ፓትርያርክ ማትያስና አጋዦቻቸው የሆኑ የዘሀሎው ተጠቃሚዎችን ሳያነሣ ውጪ አገር በስደት የሚገኙት አባቶች እንዲገቡ፣ በቤተ ክህነቱ ያለው የአንድ ብሔረሰብ የበላይነት በመጠኑ ጋብ እንዲል የጥገና ለውጥ ሊያደርግባቸው ይችላል።

ይህንን ተግባራዊ ለማድረግ በሽምግልና ስም «አንተም ተው አንተም» በሚል የሕዝብ ግንኙነት ሥራ መንግሥት የተቀሰቀሰበትን እምቢተኝነት ሊያረግቡ የሚችሉ የተለያዩ አካላትን ሚና ሊቀበል ይችላል። ተሸምግሎ ለሌሎች ሐሳብ እንደተገዛ በማስመሰል የጥገናውን ለውጥ ሊያካሒድ ይችላል። የአሸማጋይነቱን ሚና የሚጫወቱት ሰዎች በቅን ኢትዮጵያዊ መንፈስ የሚንቀሳቀሱ ያሉበትን ያህል ልባዊ ድጋፍ ለሚሰጡት የሕወሐት/ኢሕአዴግ ቡድን በምንም በምን ብለው የሕዝቡን ቁጣ በማብረድ ነገ ነጣጥሎ ለሚመታቸው አካል የሚያመቻቹም አሉበት።

በርግጥ ከዚህ በፊት በተለያዩ አጋጣሚዎች የታየ እንደመሆኑ ሽምግልና እና ሕወሐት አብረው ይሄዳሉ ተብሎ አይጠበቅም። በሽምግልና የሚመጣ ጥገናዊ ለውጥ ከፍ ብለን በቁጥር አንድ ካየነው ሑነት ብዙም የተለየ ለውጥ ሊያመጣ አይችልም። የቀለም ቅብ የመሠረት ችግር ያለበትን ቤት ከመፍረስ አይታደገውም፤ ምስጥ የበላውን ምሶሶ ቀለሙን በመቀያየር ለውድቀት ማትረፍ አይቻልም። በጥገናዊ ለውጥ የሚታለሉ ሰዎች በጥቂት ነገር የሚደለሉና ከመጀመሪያውም የነገሮችን ጥልቀት ያልተረዱ ብቻ ናቸው።

ሑነት  (Scenario) ቁጥር ሦስት

ሥር ነቀል ለውጥ

ነገሮችን በጥሙና ስንመረምራቸው አሁን የተያዘው ሕዝባዊ እምቢተኝነት እና ዝግመታዊ ለውጥ አንድ ነገር ሥር ነቀል ለውጥ እየመጣ መሆኑን በቅጡ ያመለክታል። ይህ ሥር ነቀል ለውጥ ፍፁማዊ የመንግሥት ለውጥን ሊያመጣ የሚችል ርምጃ ነው። መንግሥት የፈቀደውን ያህል መሣሪያ የታጠቀ ቢሆን፣ የፈቀደውን ያህል አሰቃቂ እመቃ እና አፈና በማድረጉ ቢገፋም፣ አንዱን ብሔረሰብ ከአንዱ ማጋጨቱ ምንም ያህል በመንግሥት ደረጃ ቢናፈስም ይህ የኅዳጣን (የጥቂቶች) መንግሥት መውደቁ አይቀርም። ምናልባት መቅረብ ያለበት ጥያቄ «መቼ?» የሚለው ነው።

ሥር ነቀል ለውጡ ይዞት የሚመጣቸው በጎ ውጤቶች እንዳለው ሁሉ ላለፉት 25 ዓመታት በተፈፀሙ አፍራሽ ተግባራት ምክንያት አገሪቱን የሚያስከፍላት ዋጋም መኖሩ ከግምት ውስጥ መግባት ይኖርበታል። ሕወሐት የተደራጀ ኃይል እንደመሆኑ በአንድ ጊዜ ብን ብሎ ሊፈርስ የሚችል አይደለም። ነገር ግን መንግሥታዊ ሥልጣንን ተቆናጥጦ ለመቆየት ሕዝቡ አልገዛም ከማለቱ የተነሣ «ቤዝ« ወደሚለው የትግራይ ግዛት ሊያፈገፍግ ይችላል። ብዙዎቹ መሪዎቹና ደጋፊዎቹም ንብረታቸውን ወደማሸሽ፣ አገር ጥለው ወደመሸሽ ሊገቡ ይችላሉ። የዚያ ምልክቶች መታየት ከጀመሩ መቆየታቸውን ልብ ይሏል።

ሕወሐት ወደ ቤዙ ማፈግፈግን ከመረጠ (ደርግ ትግራይንና ኤርትራን ለቅቆ ሲወጣ እንዳደረገው) በሰላም፣ ያለምንም ውድመት ይወጣል ብሎ መገመት የዋህነት ይሆናል። ከዚህ ቀደም በመሐል አዲስ አበባ ሳይቀር ፍንዳታዎችን በማቀነባበር «አሸባሪዎች ፈጸሙት» እንዳለውና ከጥቂት ሳምንታት በፊትም በመተማ ይኖሩ የነበሩ የትግራይ ተወላጆችን የዘር ፍጅት እንደደረሰባቸው በማስመሰል በደኅንነቱ በኩል እንዳሰደዳቸው ሁሉ (http://wazemaradio.com/?p=2853)፣ አሁንም በትግራይ ሕዝብ ንብረቶች እና ሕይወት ላይ እንዲሁም በተቀረው ኢትዮጵያዊ ዜጋ ንብረቶች ላይ ውድመት ሊቃጣ ይችላል የሚል ስጋት አለ። «ባልበላው ጭሬ ላፍሰው» የሚለው ተረት በተግባር ሲውል ስላየን ይህንን አለመጠበቅ የዋሕነት ይሆናል። ጥያቄው ለዚያ ጊዜ ያለን ዝግጅት ምንድነው የሚለው ብቻ ነው።

የሕወሐት የብረት አገዛዝ መላላት ብቻ ሳይሆን መሰባበር ሲጀምር ይኸው ቀውስ የንጹሐን ወገኖችን ሕይወት የሚያበላሽ እንዳይሆን በተለይም ቤተ ክርስቲያን እና ቤተ ክርስቲያንን የመሳሰሉ ተቋማት ትልቅ ኃላፊነት አለባቸው። ሕወሐት በደህና ጊዜ መንግሥታዊ ያልሆኑ ተቋማትን በማሽመድመዱ ምክንያት እና ማኅበረሰባዊ ሰንሰለቱ ባይበጠስም እንዲቀጥን በማድረጉ ለዚህ ዓይነቱ ክፉ ጊዜ ይጠቅም የነበረውን ማኅበራዊ ካፒታል አባክኖታል። ስለዚህም ለችግር ጊዜ መድረስ ይገባት የነበረችው ቤተ ክርስቲያን ያንን ሰማያዊ ኃላፊነቷን ልትወጣ የምትችልበትን አቅም አድክሞታል። መሪዎቿ በመለካዊነት የተጠመቁ በመሆናቸው ምክንያት የአስታራቂነትን እና የአረጋጊነትን ሚና ሊጫወቱ የሚችሉበት ዕድል በእጅጉ ተመናምኗል። በሕዝቡ ዘንድ ያላቸው ተቀባይነት የተጎዳ በመሆኑ ቃላቸውን ሊሰማ የሚችል ሰው ማግኘት ከባድ ይሆናል። ከሕዝብ ጋር አብሮ ችግርን መካፈል፣ ስቃዩን መሰቃየት፣ ኃዘኑን ኃዘን ማድረግ የሚጠቅመው ለዚህ ዓይነቱ ክፉ ጊዜ ነበር።

ሕወሐት ሥልጣኑን ሲለቅ አሜሪካዊው ፓትርያርካችን ዜግነት ወደተቀበሉበት አገር መመለሳቸው የማይቀር ነው። እሳቸውም በተራቸው የስደት ሲኖዶስ፣ የስደት አስተዳደር፣ የስደት ካህናት ወዘተ ወዘተ ይዘው ይቀጥላሉ። በስደት አገር በሕዝቡ ላብ የተቋቋሙት አብያተ ክርስቲያናት ሰላም እና አገልግሎት በዚህ አይታወክም ብሎ መገመት የዋሕነት ነው። የዘመናችን ክፉ ፖለቲካ በአስተሳሰብ ላይ የተመሰረተ ሳይሆን በአገር ልጅነት፣ በብሔረሰብ እና በቋንቋ ላይ የቆመ እንደመሆኑ የአብያተ ክርስቲያናቱም አሰላለፍ ያንን መከተሉ የሚጠበቅ ነው። ከዚህ በፊት የተሞከረ እንጂ አዲስ ነገርም አይደለም። እውነታውን ላለመመልከት ዓይናችንን ካልጨፈንን በስተቀር።

አገሪቱ መሠረታዊ ለውጥ ስታደርግ የቤተ ክርስቲያን አስተዳደርም ሥር ነቀል ለውጥ ይጠብቀዋል። ፓትርያርክ ማትያስና አጋሮቻቸው ስደትን መረጡም አልመረጡም በስደት ላይ የነበሩት አባቶች በፈንታቸው በኅብረትም ይሁን በየግላቸው ወደ አገራቸው መግባታቸው የሚጠበቅ ነው። ከ25 ዓመታት በላይ ከቤተ ክህነቱ አስተዳደር ተለይተው እንደመቆየታቸው የተሰደዱት ሲመለሱ በአገር ውስጥ ካለው ጋር ያለ ምንም ችግር ተዋሕደው አገልግሎታቸውን እንዲፈጽሙ ምን ሊደረግ ይገባል? በዚህ 25 ዓመት በቤተ ክርስቲያን ላይ ወንጀል የፈፀሙ፣ ንብረቷን የዘረፉ ሰዎች አሉ። አስተዳደራዊ ብቻ ሳይሆን ሌሎች ወንጀሎች ተፈጽመዋል። የነበረው እንዳልነበር ሆኗል። ሥር ነቀሉ ለውጥ የበለጠ መተረማመስና ዝርፊያ የነገሠበት እንዳይሆን ዝግጅት እስካልተደረገ ድረስ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ ለሚሉ ወንጀለኞች በር መከፈቱ አይቀርም።

እንግዲህ ዞሮ ዞሮ ጥያቄው ለቤተ ክርስቲያን አባቶች፣ ለሊቃውንቱ፣ ለምእመናኑ እና ጉዳዩ ለሚመለከታቸው የኢትዮጵያ ልጆች ሁሉ ነው። አገራችን ላይ እየመጣ ያለውን ሑነት አስመልክቶ ምን ያህል ተዘጋጅተናል? የዳር ተመልካቾች ሆነን እንቅር ወይንስ በአገራችን ጉዳይ ወሳኝ ሚና እንጫወት? ጥቂት ግለሰቦች ከደም አፍሳሹ መንግሥት ጋር ወግነው በሚፈጽሙት በደል የቤተ ክርስቲያናችን ታሪክ በሙሉ በዚህ ጥቁር ነጥብ ይበላሽ ወይንስ ይህንን የሚክስ ተግባር እንፈጽም? እዚህም እዚያም በግላችን እንጩህ ወይንስ በቤተ ክርስቲያን ልጅነታችን ለአገራችን በአንድነት ድምጻችንን እናሰማ? ታሪካዊው ጥያቄ ቀርቦልናል። መልሳችን ይጠበቃል። ይቆየን

ማህበረ ቅዱሳንን በመደገፍ ታላቅ እና ደማቅ የአጋርነት ንቅናቄ ሊደረግ ነው!

By ቀሲስ ሳህለማርያም

ንቅናቄው በጩሐት ሳይሆን ብልሃት እና ብስለት የተሞላበት መሆኑ ታውቋል።

image

የኢሕአዴግ መንግስት እና በቤተክህነት ውስጥ የተሰገሰጉ ካድሬዎች የተዋህዶ እምነትን የፖለቲካ አሽከር ለማድረግ የጀመሩትን ሴራ እና በማህበረ ቅዱሳን ላይ የተሰነዘረውን የስም ማጥፋት ዘመቻ በመቃወም በድምጻችን ይሰማ ዘኦርቶዶክስ እና በእኔም ለእምነቴ በብስለት እና ብልሃት በተሞላበት ሁኔታ በጋራ የተዘጋጀ ታላቅ እና ደማቅ የአጋርነት ንቅናቄ ማህበረ ቅዱሳንን በመደገፍ ሊካሄድ እንደሆነ እና ምእመናን ለዚሁ ንቅናቄ እንዲዘጋጁ ጥሪው ተላልፏል።
===============================
የመጀመሪያው ዙር ዝርዝር መግለጫ እንደሚከተለው ነው።

ለማኅበረ ቅዱሳን እመሰክራለው :: ለቀጣዩ የአደባባይ ምስክርነት በተጠንቀቅ እንዘጋጅ።
ምእመናን ምን ማድረግ እንዳለብን በቀጣይ ቀናት የሚገለፅ ይሆናል፡፡

††† #ድምጻችንይሰማዘኦርቶዶክስ – #እኔም_ለእምነቴ ! ††† የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆነ እና ስለማኅበረቅዱሳን በጎ ሥራ ለመመስከር እንዲቻል ይህ መልዕክት ለሁልም ማዳረስ ሐይማኖታዊ ግዴታችን ነው ፡፡

በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን !
እኔም ለእምነቴ የማህበራዊ ድረ ገፅ ተጠቃሚ ምንጮቻችን መሰረት፤ በማኅበረቅዱሳን ላይ አሁን እየተፈፀመ ያለው የስም ማጥፋት እና ውግዘት፤ ገና ከጥንስሱ ከማንም በፊት መረጃው ለሁሉም እንዲደር ጥረት ተደርጓል፡፡

ይሁን እንጂ ያስተላለፍ ነው መልዕክት ከቁምነገር ሳይቆጠር አብዛኛው ሰው ጉዳዩን በቸልታ አልፏታል፡፡ ሆኖም ግን በእኔም ለእምነቴ መረጃው ከተላለፈ ከ1 ቀን በኋላ ሪፖርተር ጋዜጣ በጉዳይ ዙሪያ ሰፊ ዘገባ ይዞ ወጥቷአል፤ ከዚያ ቀን ጀምሮ እስካሁን ስለማኅበረ ቅዱሳን መልካም የሆነ ነገር እየተሳማ አይደለም፡፡

የማኅበረ ቅዱሳን ጉዳይ አሁን ላይ ከጫፍ የደረሰ አሳሳቢ የቤተክርስቲያናችን ጭንቀት ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳን በኢትዮጵያ ኦርቶዶክ ተዋሕዶ ቤተ/ክ እጅግ በጣም ለቁጥር የሚታክት መንፈሳዊ አገልግሎት የሰጠ እና እየሰጠ የሚገኝ መኅበር ነው፡፡

ይሁንእንጂ ጥቅምት፯ቀን፳፻፯ዓ.ም. በጠቅላይ ቤተክህነት የስብሰባ አዳራሽ በተጀመረው ፴፫ኛው የመንበረ ፓትርያርክ አጠቃላይ ሰበካ መንፈሳዊ ጉባኤ ዓመታዊ መደበኛ ስብሰባ ላይ የጉባኤ መክፈቻ ቃለ በረከት እንዲሰጡ የተጋበዙት ፓትርያርክ አባማትያስ፣ ማኅበረቅዱሳንን ‹‹የቤተ ክርስቲያን ቅኝገዥ›› ነው ፣ ‹‹እኔ ብቻዬን የምሠራው ነገር የለም፤ በዚኽ መግለጫ እንድትሠሩበት ነው የምነግራችኹ፤ አባ ማትያስ አላበደም፤ መልእክቴን እያስተላለፍኹ ነው ያለኹት፤መልእክቴን ተቀበሉ ብዬ እማፀናችኋለኹ፡፡››አስከትለውም ‹‹ቤተክርስቲያን ከቅኝ ተገዥነት ትውጣ፤ ካህናቱ ከመከራ ይውጡ›› በማለት በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የመጨረሻ አስደንጋጭ እና አሳዛኝ ትዕዛዘቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በመሆኑም የፊታችን እሁድ ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓም በቅድስትሥላሴ ካቴድራል ቤተ/ክ “ዝክረ አቦ ሊቀነጳጳሳት” መንፈሳዊ መራሃ-ግብር ይካሄዳል፡፡ በዕለቱም የአባጳውሎስ የሐውልት ምረቃ ይደረጋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ ነገር ግን የዚህ መረሃ-ግብር ዋንኛ ዓላማ ቀደምት ቅዱስ ጳጳሳት እና ብፁዓንሊቃነጳጳሳትን በሥጋሞት የተለዩትን በማስብ የፀሎት እና የፍትሐት ስነ-ስርዓት ይደረጋል፡፡

ይህም የሚሆነው የቅ/ሲኖዶሱ ዓመታዊ ስብሰባ ከመካሄዱ የመጀመሪያው እሁድ ነው፡፡ እንዲህ ዓይነቱ መንፈሳዊ መረሃ-ግብር ከ1998 ዓ.ም ጀምሮ እየተካሄድ የሚገኝ ነው፡፡
ስለዚህም የፊታችን እሁድ ጥቅምት 9 ቀን 2007 ዓም በቅድስት ሥላሴ ካቴድራል ቤተ/ክ ከሥርዓተ ቅዳሴ በኋላ፤ ፓትርያርክ አባ ማትያስ፣ በአገር ውስጥ እና በውጪ የሚገኙ በሙሉ ብፁዓን ሊቃነጳጳት፣ የአዲስ አበባ ሀገረስብከት ገዳማትና አድብራት አስተዳደሪዎች እና ፀሐፊዎች እንዲሁም ጥሪ የተደረገላቸው የውጪሀገር ብፁዓን ሊቃነጳጳሳት በሚገኙበት ታላቅ መንፈሣዊ ፕሮግራም ይካሄዳል፡፡

በዕለቱ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆነ ሁሉ በመረሃ-ግብሩ የመሣተፍ ሓይማኖታዊ ምግባር ነው፡፡ በዚህ ታላቅ ሐይማኖታዊ መረሃ-ግብር የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ በሙሉ መገኘት አለብን፡፡ በዕለቱም ስለማኅበረ ቅዱሳን ባለፉት 17 ዓመታት ማኅበሩ በቤተክርስቲያናችን የሰጠው መንፈሳዊ አገልግሎት እንጂ ‹‹የቤተክርስቲያን ቅኝ ገዥ›› አለመሆኑ የምንመሰክርበት መልካም አጋጣሚ ነው፡፡

በዕለቱም ምእመናን ምን ማድረግ እንዳለብን በቀጣይ ቀናት የሚገለፅ ይሆናል፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት ተከታይ የሆነ እና ስለማኅበረቅዱሳን በጎ ሥራ ለመመስከር እንዲቻል ይህ መልዕክት ለሁልም ማዳረስ ሐይማኖታዊ ግዴታችን ነው ፡፡

ወስብህትለእግዚአብሔር !!!

ማኅበረ ቅዱሳን እንዴት ወዳጆች አፈራ? ጠላቶችስ ለምን ተነሡበት?

Eotcmk.org

“ምንም እንኳ በለስም ባታፈራ፥ በወይንም ሐረግ ፍሬ ባይገኝ…በእግዚአብሔር ደስ ይለኛል ትን.ዕንባ.3፡17-19”

image

በእግዚአብሔር ፈቃድ በቅዱስ ሲኖዶስ ይሁንታ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ለመደገፍና ለማጠናከር የተመሠረተው ማኅበረ ቅዱሳን ከተቋቋመበት ጊዜ ጀምሮ አያሌ ፈተናዎችን እያሳለፈ 22 ዓመታት ተጉዟል፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በዓመታት ጉዞው ባከናወናቸው መልካም ተግባራት ታላላቅ የቤተክርስቲያን አባቶችን ጨምሮ እጅግ በርካታ ወዳጆችን እንዳፈራ ሁሉ ጥቂት በተቃራኒው የቆሙ ስሙን በየጊዜው በክፉ የሚያነሱ ቡድኖችም ተነሥተውበታል፡፡

ወዳጆቹ የቤተ ክርስቲያን ወዳጆች ናቸውና በአገልግሎቱ ተማርከው በሚሠራቸው መልካም ሥራዎች ተስበው ቤተ ክርስቲያን ያለባትን የአገልግሎት ክፍተት ለመሙላት በጋራ ከማኅበሩ ጋር በመሥራት ሲተባበሩ፤ በአንጻሩ ጠላቶቹ ደግሞ የተለያዩ አጋጣሚዎችን እያስታከኩ ማኅበሩን ለመወንጀል እየተጣጣሩ ይገኛሉ፡፡

 

ማኅበረ ቅዱሳን እንዴት ወዳጆች አፈራ? ጠላቶችስ ለምን ተነሡበት?

ማኅበረ ቅዱሳን እግዚአብሔር ፈቅዶ ከተመሠረተበት ጊዜ አንሥቶ ወጣቶችን በተለይም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከመደበኛው ትምህርታቸው ጎን ለጎን በየአካባቢው ወደሚገኙ አጥቢያ አብያተ ክርስቲያናት ሔደው መሠረታዊውን የቤተ ክርስቲያን ትምህርት እንዲማሩ በማድረግ ሃይማኖታቸውን ጠንቅቀው እንዲያውቁና ቤተ ክርስቲያናቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም በዕውቀታቸው፣ በገንዘባቸውና በጉልበታቸው እንዲያገለግሉ በማድረግ፤ በተጨማሪም ወጣቱ ሀገሩንና ሕዝቦቿን አክባሪ፣ በሥነ ምግባር የታነጸ እንዲሆን በማስቻሉ ብዙ ወዳጆችን አግኝቷል፡፡

 

ከዚህም ሌላ የመናፍቃኑንና ቤተ ክርስቲያኒቱን እናድሳለን ብለው የተነሡትን የመናፍቃኑ ተላላኪ ቡድኖችን ሴራና የአክራሪ እስልምናውን እንቅስቃሴ በመረጃ አስደግፎ በማጋለጡ፣ ከክፉ ትምህርታቸው መመለስ ያልፈለጉ የተሐድሶ ቡድን አባላት ከቤተ ክርስቲያን እንዲወጡ ስለተወሰነባቸው እና ሌሎችንም የቤተ ክርስቲያኒቱን ችግሮች እየተከታተለ ለዕድገቷና ለብልጽግናዋ በመሥራቱ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ የቤተ ክርስቲያን ወዳጆችን አፍርቷል፡፡

 

ከዚህ በተቃራኒው የተሰለፉት ወገኖች ደግሞ ወጣቱን እንደጠፍ ከብት ወደ ማያውቀው የመናፍቃን አዳራሽ የመንዳት ልምዳቸው በመቋረጡና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በመግባት የሚያደርጉት ሥርዓቷን የማፋለስ እንቅስቃሴ፤ እንዲሁም አገልጋዮቿንና ምእመናኖቿን የማስኮብለሉ አካሔድ ማኅበሩ በክትትል በተለያዩ መረጃዎች ስለገለጠባቸው ማኅበረ ቅዱሳንን በጠላትነት በማየት ማኅበሩ እንዲፈርስ የማይቧጥጡት ዳገት የማይፈነቅሉት ድንጋይ የለም፡፡

 

እነዚህ የቤተ ክርስቲያን የውስጥ ጠላቶች ለጥቂት ጊዜ ጋብ ብለው የነበሩ ቢሆንም አሁን ባገኙት አጋጣሚ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እንጀራዋን እየበሉ የሚኖሩ ወዳጆቻቸውን በማጠናከርና በማስፋፋት በሚሊዮን የሚቆጠር በጀት ከወዳጆቻቸው ተመድቦላቸው የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓት ለማዛባትና በጎቿን ለመበታተን ሌት ከቀን እየሠሩ ነው፡፡

 

ይኼ ዕቅዳቸው የሚሳካው እንደ ማኅበረ ቅዱሳን ያሉ ለቤተ ክርስቲያኒቱ እምነትና ሥርዓት መጠበቅ የሚቆረቆሩ ማኅበራትን ባገኙት አጋጣሚ ሁሉ አጀንዳ በማድረግና እንዲበተኑ ክፉ ሥራ በመሥራት ነው፡፡ እነዚህ የቤተ ክርስቲያን ጠላቶች ይሔንን ከንቱ ቅዠታቸውን እውን ለማድረግም በቤተ ክርቲያኒቱ የተለያየ ሓላፊነት ላይ የሚገኙትን የዓላማቸው አስፈጻሚዎች ሁሉ እየተጠቀሙ እንደሚገኙም ይታወቃል፡፡

 

ከዚህም ሌላ ድብቅ ዓላማቸው እንዲሳካ ተላላኪዎቻቸው በቤተ ክርስቲያኒቱ ሥር የሚሆን ነገር ግን ስውር ዓላማ ያለው ማኅበር እንዲመሠርቱና ከዚህ በፊት ከንቱ ተግባራቸው ታውቆ በቤተ ክርስቲያኒቱ ታግደው የነበሩ ማኅበራት ሁሉ ከሞቱበት እንዲቀሰቀሱ እየሠሩም እያደረጉም ይገኛሉ፡፡

 

በቤተ ክርስቲያን ስም ድብቅ ዓላማቸውን ለማስፈጸም ያቋቋሟቸውና የሚያቋቁሟቸው፣ ማኅበራትንም ሕጋዊ ዕውቅና ለማሰጠት እንዲያመቻቸው ማኅበረ ቅዱሳን ለቤተ ክርስቲያን አገልግሎት ከኔ ሌላ ሌሎች አያስፈልጉም የሚል አቋም ያለው ማኅበር እንደሆነ ያስወራሉ፡፡

 

በእርግጥ ማኅበረ ቅዱሳን በትክክል የቤተ ክርስቲያኒቱን ሥርዓትና ደንብ ተከትለው በሚቋቋሙት ማኅበራት ላይ የማኅበሩ ጠላቶች ከሚያወሩትና ከሚያስወሩት አሉባልታ የተለየ አቋም አለው፡፡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርቲያን የሁለት ሺሕ ዓመታት ታሪክ ያላት ጥንታዊት ቤተ ክርስቲያን ትሁን እንጂ መንበሯ ከሊቀ ጵጵስና ደረጃ ወደ ፕትርክና ለማሳደግ አንድ ሺሕ ስድስት መቶ መራራ ዓመታትን አሳልፋለች፡፡ በዚህ ማለፏ ደግሞ ሌሎች አኀት አብያተ ክርስቲያናት የደረሱበት ዘመናዊ የአደረጃጀት ደረጃ ላይ ለመድረስ አልቻለችም፡፡ ልጆቿንም ጊዜው በሚጠይቀው መንገድ ለመምራት ሳትችል ስለቆየች እነዚህን ክፍተቶች የሚሞሉ አንድ አይደለም በርካታ ማኅበራት እንደሚያስፈልጓት ማኅበረ ቅዱሳን ያምናል፡፡ ነገር ግን እኩያኑ እንደሚሉት ሳይሆን እነዚህ ማኅበራት ሲቋቋሙ ለአንዲት ቤተ ክርስቲያን ዕድገትና የአገልግሎት ሥምረት የሚንቀሳቀሱ ተልእኮአቸውና ዓላማቸው ተለይቶ የሚታወቅ፣ መንፈሳዊ ተግባርን ብቻ የሚፈጽሙ፣ የሚናበቡና በስልት ለአንድ ውጤት የሚተጉ ሊሆኑ ይገባቸዋል የሚል ጽኑ አቋም አለው፡፡

 

ይሔንን አቋሙን ደግሞ በርካቶች የሚደግፉት እንደሆነ ማኅበረ ቅዱሳን ያምናል፡፡ ምክንያቱም እነዚህ የመናፍቃኑ ተላላኪዎች በቤተ ክርስቲያን ስም ያቋቋሟቸው ማኅበራት ከዚህ በፊት በቤተ ክርስቲያን ላይ ጥለውት የሔዱት ጠባሳ የሚታወቅ ስለሆነ ማኅበረ ቅዱሳን በማኅበራት ላይ ግልጽ አቋም አለው፡፡ ከዚህም ሌላ እነዚህ የውስጥ ዐርበኞች ይኽ ስውር ዓላማቸው ያልታወቀባቸው ይመስል ማኅበሩን ለመወንጀል የማይለጥፉለት ታፔላ፣ የማይለፍፉት ወሬ የለም፡፡ ነገር ግን እነዚህ የቤተክርስቲያን ጠላቶች ስለማኅበሩ የሚያወሩት ሁሉ ከእውነት የራቀ እና ሁሉም የሚገነዘበው ግልጽ እውነታ መሆኑን ባለማወቃቸው እናዝናለን፡፡

 

ማኅበረ ቅዱሳን ምንም ስውር ዓላማ የለውም፤ ከማንኛውም የፖለቲካ አስተሳሰብ የጸዳና በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተሰጠው መተዳደሪያ ደንብና መመሪያን ሳያዛንፍ እየሠራ ያለ፤ በተሰጠውም መተዳደሪያ ደንብና ሓላፊነት መሠረት ከአባላቱ የሰበሰበውን የገንዘብ መዋጮ ገቢና ወጪ እያሰላ በውስጥ ኦዲተሮችም እያስመረመረ በመሥራት ተጨባጭ ለውጥ ያመጣ ማኅበር እንጂ በወሬ የሚኖር አይደለም፡፡ ይሔንን አሠራሩንም ቀርቦ ማየት ይቻላል፡፡ አባላቱም በገንዘባቸው፣ በዕውቀታቸው በጉልበታቸውና በመላ ሕይወታቸው ቤተ ክርስቲያንን የሚያገለግሉ እንጂ እንደ መናፍቃኑ ተላላኪዎች ለሆዳቸው ያደሩ፣ ሆዳቸው አምላካቸው የሆነባቸው እዚህም እዚያም ደሞዝ የሚቀበሉ አይደሉም፡፡

 

ማንኛውም አካል እንዲያውቅልን የምንፈልገው ሐቅ ማኅበረ ቅዱሳን ቅዱስ ሲኖዶስ ለሰጠው ሓላፊነትና አባላቱም ለገቡለት ቃል ኪዳን ሃይማኖታቸው የሚፈቅደውን መስዋዕትነት ለቤተ ክርስቲያን ልዕልናና ክብር ለመክፈል የተዘጋጁ እንጂ በተዛባ አመለካከት ወደ ኋላ የሚያፈገፍጉ አለመሆናቸውን ለመግለጽ እንወዳለን፡፡

 

ማኅበረ ቅዱሳን አገልግሎቱ የሚታይ አሠራሩም ግልጽ ነው፡፡ ስለዚህም የመናፍቃኑ ተላላኪዎች መሠረተ ቢስ ውንጀላ ከአገልግሎታችን አንዲት ጋት ወደ ኋላ እንደማይመልሰን እንዲታወቅልን እንፈልጋለን፡፡ ርእይና ተልእኮአችንን ለማሳካት ዛሬም ነገም እንሠራለን፤ ትናንትን ያሻገረን እግዚአብሔር ዛሬንም ያሳልፈናልና፡፡

ይህ ጽሑፍ ግንቦት 16 ቀን 2003 ዓ.ም ወጥቶ የነበረና ታርሞ በድጋሚ የቀረበ ነው፡፡

 

የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ እወቁ፡፡ያዕ1፡2

ማኅበረ ቅዱሳን

image

ቅድስት ቤተ ክርስቲያን የተዋጀችውና የተመሠረተችው መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መከራ ተቀብሎ፣ ሥጋውን ቆርሶ፣ ደሙን አፍስሶ ነው፡፡ ሐዋ.2ዐ፥28፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ይህንን ሲገልጽም “በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ።” ብሏል፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን በደሙ ሲዋጅ ጥንተ ጠላት ዲያቢሎስን ድል ነስቶ፣ ምርኮውን መልሶ፣ ሞትን ደመስሶ በመሆኑ ዲያቢሎስ የድል ነሺውን ቤተ ክርስቲያንና ወደ ነጻነት የተመለሱትን ክርስቲያኖች ዘወትር ይፈትናቸዋል፡፡

ቅዱስ ዮሐንስ ወንጌላዊው እግዚአብሔር ኃላፊያቱንና መጻእያቱን በገለጸለት ራዕይ ስለ ዲያቢሎስ ፈተና ሲጠቁም “ዓለሙንም ሁሉ የሚያስተው ዲያብሎስና ሰይጣን የሚባለው ታላቁ ዘንዶ እርሱም የቀደመው እባብ ተጣለ፤ ወደ ምድር ተጣለ ….ለምድርና ለባሕር ወዮላቸው፤ ዲያብሎስ ጥቂት ዘመን እንዳለው አውቆ በታላቅ ቍጣ ወደ እናንተ ወርዶአልና። ዘንዶውም ወደ ምድር እንደ ተጣለ ባየ ጊዜ ወንድ ልጅ የወለደችውን ሴት አሳደዳት።” ዮሐ. ራዕ. 12፥9-17፡፡

ታሪክና መጻሕፍት እንደሚያስረዱት ቤተ ክርስቲያን ከተመሠረተችበት ጊዜ ጀምሮ ከፈተና ተለይታ አታውቅም፡፡ ጌታን የሰቀሉ አይሁድ ደቀመዛሙርቱን በእርሱ ስም እንዳያስተምሩ ለማድረግ በማስፈራራት ብዙ ጥረዋል፤ አስረዋቸዋል፣ ገርፈዋቸዋል፣ አሳደዋቸዋል፣ ገድለዋቸዋል፡፡ ሐዋ.ሥ 4፥17-21 ነገር ግን ቤተ ክርስቲያን በአለት ላይ የተመሠረተችና በመንፈስ ቅዱስ የምትመራ ስለሆነ ሥራዋ አልተቋረጠም፤ ተከታዮቿም አልጠፉም ዕለት ዕለት ይበዛሉ እንጂ፡፡ ማቴ. 16፥18

ቤተ ክርስቲያን በዘመነ ሐዋርያት፣ በዘመነ ሰማእታትና በዘመነ ሊቃውንት እንደጊዜው የተለያየ መከራና ፈተና አሳልፋለች፡፡ የቤተ ክርስቲያን ጠላት የሆነው ዲያብሎስ ጥንት በአይሁድ፣ በሮማዊያን ነገሥታት፣ በአህዛብ እያደረ፤ ክርስቲያኖች በሃይማኖታቸው በመጽናታቸውና ቤተ ክርስቲያንን በማገልገላቸው ሰውነታቸው በሰም ተነክሮ በእሳት እንዲቃጠሉ፣ በቁርበት ተጠቅልለው ለአንበሳ እንዲሰጡ፣ በድንጋይ ተወግረው እንዲሞቱ፣ በስለት እንዲቀረደዱ፣ በሰይፍ እንዲቀሉ ያስደርግ ነበር፡፡ ክርስቲያኖችም በእምነታቸው እየጸኑ ከሞት የተረፉት፤ በዋሻ በግበበ ምድር እየሆኑ የቤተ ክርስቲያንን አገልግሎት ሲፈጽሙ ኖረዋል፡፡ ጌታ “የሲዖል ደጆች አያናውጧትም” ያላት ቤተ ክርስቲያን እስከ ዓለም ዳርቻ እየሰፋች የመሰረታትን ጌታ እያመሰገነች ትኖራለች፡፡ ቤተ ክርስቲያን አገልግሎቷን ለማሳካትና የዲያቢሎስን ሽንገላ ለመቋቋም በተለያዩ የአገልግሎት መስኮች ልጆቿን ታሰማራለች፡፡

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን እውቅና ሰጥታ ልጆቿን ለአገልግሎት ካሰማራችባቸው መንገዶች አንዱ የማኅበራት አገልግሎት ነው፡፡ በዚህ የማኅበራት አገልግሎት የዲያቢሎስን ፈተናና ሽንገላ ተቋቁመው በርካታ መንፈሳዊ ተግባራትን እያበረከቱ ከሚገኙ ማኅበራት መካከል ማኅበረ ቅዱሳን አንዱ ነው፡፡

ማኅበረ ቅዱሳን በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ ከ22 ዓመታት በፊት ቅርጽ ይዞ የተዋቀረና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ አገልግሎቱን የሚፈጽምበት ደንብና ሥርዓት የተበጀለት ማኅበር ነው፡፡ አባላቱም የቤተ ክርስቲያኒቱ ልጆች የሆኑና በየአጥቢያቸው የልጅነት ግዴታቸውን እየተወጡ የሚገኙ ሲሆኑ በቅናተ ቤተ ክርስቲያን ተሰባስበው ለቤተ ክርስቲያን እድገት የሚያግዙ የትሩፋት ሥራዎችን የሚሠሩ ናቸው፡፡

ማኅበሩ በመተዳደሪያ ደንቡ ላይ ተለይቶ በተሰጠው ተግባር መሰረት፤ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚማሩ ተማሪዎችን በየአጥቢያቸው አሰባስቦ፤ ከየሰንበት ትምህርት ቤቶቹ ጋር በመተባበር ትምህርተ ሃይማኖትን የሚያስተምር፣ አባላቱንና በጎ አድራጊ ምእመናንን በማስተባበር ስብከተ ወንጌል በሀገር ውስጥና በውጪው ዓለም እንዲስፋፋ የሚያደርግ፣ አድባራትና ገዳማት በልማት ራሳቸውን እንዲችሉ የሚያደረግ፣ የቤ ተክርስቲያናችን ሀብት የሆነው የአብነት ትምህርት እንዲጠናከርና ሊቃውንቱም ወንበራቸውን እንዳያጥፉ በመርዳት ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ ይገኛል፡፡

ይህ መንፈሳዊ ተግባር በቤተ ክርስቲያን በመተግበሩ፤ ቤተ ክርቲያንን የማይወዱና ውድቀቷን እንጂ ጥንካሬዋን የማይሹ አካላት የማኅበሩን አገልግሎት አልወደዱትም፡፡ ስለሆነም ቤተ ክርስቲያንን ለማዳከም ማኅበረ ቅዱሳንን ጠልፎ መጣል እንደ ዋነኛ ስልት አድርገው ቆርጠው መሥራት ከጀመሩ ውለው አድረዋል፡፡ እነዚህ አካላት ለዓላማቸው የሚጠቅም ሆኖ እስካገኙት ድረስ ማንኛውንም ነገር ይጠቀማሉ፡፡ በተለያየ ደረጃ ያሉ ሰዎችን በማሳሳት፣አሉባልታ በመንዛት፣የቤተ ክርስቲያን አባቶችን ጭምር በማሳሳት የሚፈልጉትን ተግባር ለመፈጸምና ለማስፈጸም ይተጋሉ፡፡ ማሩን በማምረር ወተቱን በማጥቆር- ደጋግመው እየወተወቱ ብዙ የዋሐንን የነርሱን የማደናቀፍ ተግባር ተባባሪ ለማድረግ ይጥራሉ፡፡

በጎ ነገር ሲሠራ በጠላት ዲያብሎስ በኩል እንቅፋት እንደሚቀመጥ ሁልጊዜ የታወቀ ነው፡፡ ፈተናውን ማለፍ መሰናክሉን መቋቋም ግን የአንድ ክርስቲያን ግዴታ ነው፡፡ ማኅበረ ቅዱሳንም እንደነዚህ ዓይነት ፈተናዎች ከቀድሞ ጀምሮ ሲያጋጥሙት ቢቆይም በአገልግሎቱ ምክንያት የመጡ መሆናቸውን በመገንዘብ በአባቶች ጸሎት፣ በእግዚአብሔር ኃይል አሸንፎ ላለንበት ዘመን ደርሷል፡፡ ወደፊትም በእግዚአብሔር ፈቃድ ይቀጥላል፡፡

ከላይ በጠቀስናቸው አካላት አማካኝነት አንዳንድ ወገኖቻችን ስለማኅበሩ የተሳሳተ መረጃ ሲደርሳቸው ቤተ ክርስቲያንን የጠበቁ መስሏቸው አገልግሎቱን የሚያደነቅፉና ጥሩ ባልሆነ ሁኔታ የሚፈርጁትን አካላት ወግነው ሲቆሙ ይታያሉ፡፡ እነዚህ አካላት ትክክለኛውን መረጃ ቢያገኙ፣ ቢያውቁና ቢገነዘቡ ከማኅበሩ ጋር የዓላማ ልዩነት ስለሌላቸው፤ አብሮ በፍቅር ቤተ ክርስቲያንን ለማገልገል ምንም የሚቸግራቸው ነገር የለም ብለን እናምናለን፡፡ ወደፊትም ከማኅበሩ ጋር አብረው ሊሠሩ የሚችሉ፣ የሚመክሩና የሚያስተካክሉ እንደሆኑ ማኅበሩ ያምናል፡፡ ካሁን ቀደምም እንዲህ ዓይኖቶቹን አካላት ባገኘ ጊዜ ሁሉ ማኅበሩ በማወያየቱና በማስረዳቱ የማኅበሩን አገልግሎት እየደገፉ የሚገኙ በርካታ ናቸው፡፡

ቤተ ከርስቲያንን በዓላማ የሚጠሉ ግን የማኅበሩን አገልግሎት ቢያውቁና ቢረዱትም የዓላማ ልዩነት ስላላቸው መቼም አገልግሎቱን በቀና አያዩትም፡፡ ዕለት ዕለት ለማደናቀፍ ይጥራሉ፡፡ በዚህም የተነሳ በአሁኑ ሰዓት በቤተ ክርስቲያን መዋቅር ውስጥ ሆነው ነገር ግን ቤተ ክርስቲያንን ጠልፈው ለመጣል የሚታገሉ፣ እንዲሁም ከቤተ ክርስቲያን በአፍኣ ሆነው እጃቸውን ባስረዘሙ አንዳንድ አካላት ማኅበሩ ፈተናዎች እየገጠሙት ነው፡፡

ለምሳሌም ያህል በአንዳንድ ሀገረ ስብከቶች በቅዱስ ሲኖዶስ ጸድቆ በተሰጠው የመተዳደሪያ ደንብ መሠረት በዋናነት የሚያስተባብረውን የግቢ ጉባኤ ተማሪዎች ሃይማኖታዊ ትምህርት እንዳያስተምር ሲከለክሉና ሲያቋርጡ ይታያሉ፡፡ ማኅበሩ አገልግሎት የሚሰጥባቸውን ማእከላት ቢሮዎች የሚዘጉ አንዳንድ አጥቢያዎችም ይስተዋላሉ፡፡ በተጨማሪም ማኅበሩ የሚያበረክተውን ሁለንተናዊ የቤተ ክርስቲያን አገልግሎት እንዲደናቀፍ የሚፈልጉ አካላትም በሕዝብ ጉባኤዎችና ስብሰባዎች ሳይቀር የማኅበሩን ስም እያነሱ ተገቢ ያልሆነና ማኅበሩን በፍጹም የማይገልጹ ቅጽሎችን እየሰጡ ለማስረዳት ሲሞክሩ ይስተዋላሉ፡፡

እነዚህ ለማሳያነት በተጠቀሱት የማኅበሩ ተግዳሮቶች መነሻነት በአንዳንድ ግለሰቦች አማካይነት መዋቅሮችን አላግባብ በመጠቀም የግለሰቦቹን ምኞት ከግብ ለማድረስ የሚሠሩና ጥንቃቄ ያልታከለባቸው እርምጃዎች እንጂ የቤተ ክርስቲያን ወይም የመንግሥት ውሳኔ ነው ብለን አናምንም፡፡ ስለዚህ ማኅበረ ቅዱሳን የቤተ ክርስቲያን አካል እንደመሆኑ ፈተና ስለማይለየው ስለሚያጋጥሙት ፈተናዎች በጸሎት፣ የሚመለከታቸው አካላት በማስረዳትና በመወያየት፣ እንዲሁም በመታገስ አልፎ በኢየሱስ ክርስቶስ ደም የተመሰረተችውን ቅድስት ቤተ ክርስቲያንን እግዚአብሔር እስከፈቀደበት ጊዜ ድረስ ያገለግላል፡፡

ማኅበሩ ፈተና ሲያጋጥመው መንፈሳዊ ማኅበር እንደመሆኑ መፍትሔ ለማግኘት የሚሄድባቸው መንገዶች ሁልጊዜም የታወቁ ናቸው፡፡ ችግሮች ሲመጡ ጊዜያዊና በእግዚአብሔር ኃይል በቀላሉ ሊፈቱ የሚችሉ መሆናቸውን በመረዳት በጥበብና በትዕግስት ከሚመለከከታቸው አካላት ሁሉ ጋር እየተወያየ ይፈታል፡፡ የችግር አፈታቱ ሥርዓት መንፈሳዊነትን የተከተለ በመሆኑ ሥጋዊ አስተሳሰብን ሳይጨምር ሃይማኖታዊ ፈተና ሲመጣ ማሸነፊያው ሃይማኖታዊ ኃይል ነው ብሎ ያምናል፡፡ እርሱም እግዚአብሔርን አጋዥ አድርጎ በጾምና በጸሎት በትዕግስትና በጽናት፤ እግዚአብሔርን በመጠየቅ ነው፡፡

በማርቆስ ወንጌል ላይ እንደምናገኘው፡- (ማር. 4፡37) “ብርቱ ዐውሎ ነፋስም ተነሣና ውኃ በታንኳይቱ እስኪሞላ ድረስ ማዕበሉ በታንኳይቱ ይገባ ነበር። እርሱም በስተኋላዋ ትራስ ተንተርሶ ተኝቶ ነበር፤ አንቅተውም። መምህር ሆይ፥ ስንጠፋ አይገድህምን? አሉት። ነቅቶም ነፋሱን ገሠጸው ባሕሩንም። ዝም በል፥ ፀጥ በል አለው። ነፋሱም ተወ ታላቅ ፀጥታም ሆነ። እንዲህ የምትፈሩ ስለ ምን ነው? እንዴትስ እምነት የላችሁም? አላቸው። እጅግም ፈሩና። እንግዲህ ነፋስም ባሕርም የሚታዘዙለት ይህ ማን ነው? ተባባሉ።” ይላል፡፡ በታንኳይቱ የተመሰለችው ቤተ ክርስቲያን በፈተና ልትናወጥ ትችላለች፡፡ እንዲህ ባለ ጊዜ በውስጧ ያለውን፣ ነገር ግን እኛ የድርሻችንን እስክንወጣ ድረስ የሚጠብቀውንና ዝም ያለ (የተኛ) የሚመስለውን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን በጸሎት መጠየቅ ያስፈልጋል፡፡ ፈተናን ጸጥ የሚያደርግ አምላክ እንደምናመልክ ልንዘነጋ አይገባምና ፡፡

ማኅበሩ በቤተክርስቲያንም ሆነ በማኅበራችን ዙሪያ ስላሉ ነገሮች ማንኛውንም መረጃ የሚያስተላልፈው በራሱ ሚዲያና በመተዳደሪያ ደንቡ መሠረት ሥርዓት ባለው መልኩ በሚመለከታቸው የማኅበሩ ኃላፊዎች በኩል እንደሆነ የታወቀ ነው፡፡ ከዚህ ውጭ በሆነ መንገድ የሚተላለፍ ልዩ ልዩ መረጃዎችንና ሀሳቦችን በመያዝ ማኅበሩን በተመለከተ የግል ሀሳብንና ተግባርን ማንጸባረቅ አግባብ አለመሆኑን ሁሉም አካላት ሊያውቀው ያስፈልጋል፡፡

ማኅበራችን ማኅበረ ቅዱሳን ዓላማን ግብ ያለው በመሆኑ በጊዜው በሚታዩ ጥቅመኞችና አጽራረ ቤተ ክርስቲያን ሁከት ሳንዘናጋ የወንጌል ተልእኳችንን በጥበብና በትዕግስት ከግብ ማድረስ ይገባናል እንላላን፡፡ ስለዚህ ሐዋርያው ያዕቆብ የእምነታችሁ መፈተን ትዕግሥትን እንዲያደርግላችሁ እወቁ፡፡ ያዕ.1፡2 እንዳለ ስለ እምነታችንና ስለቤተ ክርስተያናችን የምናደርገውን አገልግሎት ፈታኙ ዲያብሎስ ሊያደናቅፍ ሠራዊቶቹን ቢያሰማራም እግዚአብሔር አምላካችንን ትዕግስትንና ጽናትን እንዲሰጠን ፈተናውንም እንዲያሳልፍልን በጽናት እንለምነው፡፡- እርሱ በሰው ዘንድ የማይቻለውን እንድንችል ማድረግ ያውቅበታልና፡፡ ለዚህም የቅዱሳን አምላክ እግዚአብሔር ይርዳን፡፡

ወስብሐት ለእግዚአብሔ

ማኅበረ ቅዱሳን ታገደ

HARA ETHIOPIA ሐራ ዘኢትዮጵያ

image

ማኅበረ ቅዱሳን ታገደ፣የማህበሩ አባላት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ዕጣ ይደርሰዋል ተብሎ ይጠበቃል
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ከ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የለቀቁት በ ወያኔ የደህንነት ኃይሎች በደረሰባቸው ማስፈራራት ነው ተባለ። ማተብ በጥሱም የሚል አዋጅም በ ወያኔ ታውጁዋል።
በወያኔው ፓትርያርክ አቶ ማትያስ ፊታውራሪነት ከተለያየ አድባራት እና ገዳማት የመጡት ጥቂት በጥቅም የተገዙ የደብር አለቆች፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ሃላፊዎች፣የ አዲስ አበባ ሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተብሎ በወያኔ የተሾመው ኦህዴድን ወክሎ ወያኔ ፓርላማ ተመራጭ የሆነው አቶ በላይ መኮንን፣ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ የሚመራውና አባ ሰረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል፣ መጋቤ ካህናት ኃይለ ሥላሴ ዘማርያም፣ መዝገበ ጥበብ ቀሲስ ዮሐንስ ኤልያስ፣ኤልያስ አብርሃ እንዲሁም ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ያሉበት ቡድን ከ ሚኒስትር ዶ/ር ሺፈራው ጋር በመሆን ባቀነባበሩት ክስ ማህበሩን ወደ ማገድ እና በ አሸባሪነት የማስወገዝ ደረጃ ተሸጋግረዋል ።

የጎዳና ላይ ነውጥ ለማነሣሣት ሁከትና ብጥብጥ የሚሰብኩና የሁከትና ብጥብጥ መንገድን የሚቀይሱ ግለሰቦችና ቡድኖች የተሰባሰቡበት ነው በሚል የሀሰት ክስ የመታገድ እርምጃ የተወሰደበት ማኅበረ ቅዱሳን እስካሁን ያወጣው ምንም አይነት መግለጫ የለም። የማህበሩ የጂማ ንዑስ ማዕከል እና የዋናው ማእከል አንዳንድ አመራሮች እና አባላት ባለፉት ሁለት ቀናት በወያኔ የ ፅጥታ ኃይሎች ማዋከብ እና ፍተሻ እየተካሂደባቸው ቢሆንም ምንም አይነት መረጃ ለሚድያ እንዳይሰጡ በማህበሩ ዋና ፀሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ እንደተነገራቸው ለማወቅ ተችሉዋል ። ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ታዛቢወች ማህበሩ ለ ቤተ-ክርስቲያኒቱ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ቢሆነም የማህበሩ ጥቂት አመራሮች ግን ከወያኔ ጋር በመተባበር አሁን በ ወያኔ የተሾሙተን አቶ ማትያስ ከማስመረጥ ጀምሮ ከበስደት ሀገር ከሚገኘው በብፁዕ አቡነ መርቆርዮስ ከሚመራው ሕጋዊው ሲኖዶስ ጋር ይደረግ የነበረውን የአባቶችን የእርቅ ውይይት እስከ ማስተጉዋጎል ድረስ አፍራሽ ሚና ይጫወት እንደነበር አስታውሰዋል ። በአሁኑ ሰዓት ወያኔ በሀገራቺን ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰስ ይገኛል ። በ ወንዶምቻችን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ ያደረገውን የሐሰት ክስ አሁንም በማህበረ ቅዱሳን ላይ ሊደግመው ዝግጅቱን አጠናቆ ይገኛል ።

http://haraethiopiadotcom.wordpress.com/