አንዳርጋቸው ፅጌ እንዴት ተያዘ?

Keep reading books, but remember that a book is only a book, and you should learn to think for yourself. –Maxim Gorky

ከተስፋዬ ገብረአብ (Gadaa)

image

አንዳርጋቸው ፅጌን ለመጨረሻ ጊዜ ያየሁት የ2014 የፋሲካ በአል በዋለ ማግስት ነበር። ወደ ለንደን
መንገድ ስለነበረው ከተከዜ በረሃ ወደ አስመራ መጥቶ ሳለ ደወለልኝና ተገናኘን። ሳገኘው ታሞ ነበር። ከምግብ
ወይም ከውሃ ጋር የተያያዘ ቀላል ህመም እንደሆነ ነገረኝና ወደ ፋርማሲ ሄደን መድሃኒት ገዛን።

እየደወልኩ ስለ ጤንነቱ ስጠይቀው ቆየሁ። በሶስተኛው ቀን ተሲያት ላይ ይመስለኛል ወደ ቤቱ ብቅ
አልኩ። የግቢውን በር ገፍቼ ስገባ አንዳርጋቸው በሁለት እጆቹ ልሙጥ የባህር ድንጋዮችን ተሸክሞ ቁጭ ብድግ
እያለ ስፖርት ሲሰራ አገኘሁት። ማጅር ግንዱ በላብ ርሶአል። ግቢው ውስጥ ካለችው የብርቱካን ዛፍ ላይ
ያንጠለጠለውን ፎጣ አንስቶ ላቦቱን ማደራረቅ ያዘ።

በረንዳው ላይ ቁጭ ብለን ጥቂት ካወጋን በሁዋላ ለመሄድ ተነሳሁ። በዚህ ጊዜ ከሶስት ቀናት በሁዋላ ወደ
ለንደን ለመሄድ ትኬቱን እንደቆረጠ ገልፆልኝ በነጋታው ምሽት የራት ቆይታ እንድናደርግ ጠየቀኝ። ሁለታችንም
በጋራ የምናውቀውን ሰው ስም ጠቅሶም በራት ቆይታው ላይ እንደሚገኝ ጠቆመኝ። ተስማማሁና ቀጠሮ ያዝን።

በነጋታው በቀጠሮአችን መሰረት ተገናኘን። ምንም ልዩ ርእሰ ጉዳይ አልነበረንም። ስለ አካባቢያችን
ፖለቲካ ተጨዋወትን። ስለ ግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አንስቶም ጥቂት ነገረን። በሰው ሃይልና በአንዳንድ አስፈላጊ
ተሽከርካሪዎች በመጠናከር ላይ መሆናቸውን፣ ወያኔ ያዳከመውን የኢትዮጵያዊነት ስሜት ለመመለስ የሚሰራው
የፖለቲካ ስራ ራሱን የቻለ ጊዜ የሚወስድ ስራ እንደሆነ፣ በጥቅሉ ግን ትግሉ ተስፋ እንዳለው ነበር ያጫወተን።
ሞራሉ ጥሩ ነበር። ተስፋ የመቁረጥ ዝንባሌ አላየሁበትም።

ራት እስኪቀርብ፣ “የጀሚላ እናት” በሚል ርእስ ካዘጋጀሁት (በወቅቱ ካልታተመ) መፅሃፍ አንድ ትረካ
አነበብኩላቸው። “የአዲሳባ ቀብር” የሚል ነበር። ትረካው ኮሜዲ አይነት ስለነበር እየሳቁ ነበር ያዳመጡኝ።
ከእኩለ ሌሊት በፊት መለያየታችን ትዝ ይለኛል። አንዳርጋቸው መኪና ስላልያዘ ቤቱ አድርሼው፣ “መልካም
መንገድ” ተመኝቼ ተሰናበትኩት።

ያቺ ምሽት ከአንዳርጋቸው ጋር የመጨረሻ የምተያይባት እለት ትሆናለች ብዬ ግን እንዴት ማሰብ ይቻላል?
አሁንም ቢሆን ለዘልአለሙ አንተያይም ብዬ አልደመደምኩም። ሌላው ቀርቶ ይህች መጣጥፍ እንኳ ካለበት ጉረኖ
ደርሳ ሊያነባት እንደሚችል ተስፋ አደርጋለሁ።

ስለነገ ማንም አያውቅም። መለስ ዜናዊ ከግርማ ወልደጊዮርጊስ ቀድሞ ይሞታል ብሎ ሊያስብና ሊገምት
የሚችል ማንም አልነበረም። ደካማና በቀላሉ ተሰባሪ የሆነች ነፍሳችን ከአስር ደቂቃ በሁዋላ ምን ሊገጥማት
እንደሚችል እንኳ አናውቅም። ተስፋ ግን በልባችን ሞልቶ ተርፎአል። ስለዚህም ሰዎች በተስፋ ይኖራሉ። ሰዎች
በተስፋ አሻግረው ያልማሉ። ሰዎች በተስፋ እርቀው ይጓዛሉ…

ደጋግሜ እንደገለፅኩት አንዳርጋቸው ከነሙሉ ችግሮቹ ብርቱ ሰው ነበር። አንዳርጋቸው አደጋ ላይ
በመውደቁ ኢትዮጵያውያን “የአንድነት ሃይል” ፖለቲከኞች ትልቅ ሰው ጎድሎባቸዋል። ርግጥ ነው፣ ከአንዳርጋቸውጋር ስናወጋ የኦሮሞ ጉዳይ ከተነሳ ተግባብተን አናውቅም። አንዳርጋቸው በያዘው የፖለቲካ አቋም ከሰፊው የኦሮሞ
ህዝብ ደጋፊ ሊያገኝ እንደማይችል መናገሬም አልቀረ። በተለያዩ ፅሁፎች የማንፀባርቀውን አቋም አነሳ ነበር። አንድ
ጊዜ በወግ መሃል፣

“የታሪክ እስረኛ ላለመሆን ምኒልክ የኦሮሞ ህዝብ ላይ ለፈፀመው ግፍ ይቅርታ ጠይቃችሁ አጀንዳውን
ለመዝጋት ለምን አትሞክሩም?” ብዬ ጠይቄው በአነጋገሬ በጣም መቆጣቱን አስታውሳለሁ።

አንዳርጋቸው ለአማራ ብቻ ሳይሆን፣ ለትግራዩም፣ ለኦሮሞውም በአጠቃላይ ለመላ ኢትዮጵያውያን
የሚጠቅም የፖለቲካ መስመር ተከትያለሁ ብሎ በጥብቅ ያምናል። ለነገሩ ወያኔም እንዲሁ ይላል። ኢህአፓም
ይህንኑ ይላል። ሞአ-አንበሳ እንኳ በአቅሟ የዘውድ መመለስ ለኢትዮጵያ አንድነት ፍቱን መፍትሄ መሆኑን
ትሰብካለች። ፈላስፋው ዘርአያእቆብ እንደጠየቀን ‘ሁሉም የኔ መስመር ትክክል ነው’ የሚል ከሆነ ‘በዚህ መካከል
ማነው ፈራጅ?’ የሚል ጥያቄ ይነሳል። ምላሹ ቀላል ነበር። ፈራጅ ሊሆን የሚችለው ህዝብ ነው። የምንመፃደቅበት
ህዝብ ግን የሚሻለውን የመምረጥ እድል አላገኘም…

ሌላ ቀን ደግሞ እንዲሁ ከአንዳርጋቸው ጋር ስንጨዋወት እንዲህ አለኝ፣

“የወያኔ መውደቅ የማይቀር ነው። ከወያኔ መውደቅ በሁዋላ በአገሪቱ ሊፈጠር የሚችለው ክፍተትና
መለያየት ግን በጣም ያሳስበኛል። ከባድ ፈተና ከፊታችን ተደቅኖአል። ለብሄርና ለቋንቋ ጥያቄዎች አጥጋቢ መልስ
መስጠት ይጠበቃል። ከፊታችን የተደቀኑትን ቋጥኝ ጥያቄዎች ለመመለስ የሚያበቃ በቂ ዝግጅት አለን ለማለት ግን
እቸገራለሁ። ችግሩ ምን መሰለህ? መሬት ላይ የሚሰራው ስራ ከፕሮፓጋንዳው ጋር አልተመጣጠነም።
ፕሮፓጋንዳው መቅደሙ አደገኛ ነው።”

አንዳርጋቸው ይህን መሰረታዊ ችግር የሚዳስስና መፍትሄ የሚያስቀምጥ አዲስ መፅሃፍ በመፃፍ ላይ ነበር።
የመፅሃፉን ርእስ “ነፃነትን የማያውቅ ነፃአውጪ – ክፍል ሁለት” እንዳለውም ነግሮኝ ነበር። የመጀመሪያው “ክፍል
አንድ” መፅሃፍ፣ የአርትኦት ስራ ያስፈልገው ስለነበር፣ በአጫጭር አረፍተነገሮችና በቀላል አማርኛ እንድነካካው
ጠይቆኝ በትርፍ ጊዜዬ እያገዝኩት ነበር። ሁለቱንም መፃህፍት አንድ ላይ የማሳተም አሳብ ነበረው።

ወያኔ አንዳርጋቸውን የመን ላይ አሸምቀው እንደያዙት የሰማሁ ቀን በድንጋጤ ደንዝዤ ነበር። ማመን
አቃተኝ። አንዳርጋቸው ከአራት አመታት በላይ ወደ ኤርትራ ሲመላለስ የሱዳንና የየመንን አየር መንገዶች ተጠቅሞ
እንደማያውቅ አውቃለሁ። እኔ አልፎ አልፎ የየመንን መንገድ እንደምጠቀም ስለሚያውቅ፣ “ተው፣ አትመናቸው”
ብሎ ጭምር መክሮኛል። የመን ላይ ‘መንግስት አለ’ ለማለት እንደማይቻል አንዳርጋቸው እያወቀ ምን ሊሆን የመን
ሄደ? ያልተመለሰ ጥያቄ ሆነብኝ።

ዜናውን ስሰማ የተደበላለቀ አሳብ ወደ አእምሮዬ መጣ። ሊሆን የማይችል ጥርጣሬ ነገሮች ጭምር
ረበሹኝ። ዜናውን በሰማሁበት ደቂቃ ስንቱን አወጣሁ፤ ስንቱን አወረድኩ። ማን ዘንድ ደውዬ ማንን እንደምጠይቅ
ግራ ገባኝ። በመጨረሻ ወደ አንዳርጋቸው ዘመዶች እየበረርኩ ሄድኩ።

አስመራ ላይ አንዳርጋቸው “ዘመዶች” አሉት። የስጋ ዘመዶቹ አይደሉም። አዲስአበባ ጎረቤቶቹ የነበሩ
ናቸው። ነገሩ እንኳ ከጉርብትና በላይ ነው። አንዳርጋቸው ወጣት የኢህአፓ አባል ሆኖ ሲንቀሳቀስ የደርግ አፋኞች
ሊገድሉት ያሳድዱት ነበር። ወንድሙንና አንድ ኤርትራዊ ጓደኛውን ጎዳና ላይ ሲረሽኑበት አንዳርጋቸው የሚገባበት
ቀዳዳ አልነበረውም። በዚህ ችግር መሃል፣ የእናቱ ጓደኛ የነበረች አንዲት ኤርትራዊት ሴት አንዳርጋቸውን ወደ
አስመራ በመውሰድ ከመኖሪያ ቤቷ ሸሸገችው። ስድስት ወራት ከቤት ሳይወጣ ከቆየ በሁዋላ ያቺ ሴት የሃሰት
መታወቂያ አውጥታለት፣ ትንሹን አንዳርጋቸው እንደ ገበሬ አልብሳ ወደ ገጠር በመውሰድ ለሻእቢያ አስረከበችው።
ሻእቢያ አንዳርጋቸውን በሱዳን በኩል ሸኘው። ከዚያም አንዳርጋቸው ወደ ለንደን አቀና። አንዳርጋቸው መፅሃፉን
ሲፅፍ የመፅሃፉን መታሰቢያ ከሰጣቸው መካከል ጓደኛው የነበረ የእነዚሁ የኤርትራውያኑ ልጅ የነበረ ነው። ይህን
የተከበረ ቤተሰብ አንዳርጋቸው ወስዶ አስተዋውቆኝ ነበር። ስድስት ወራት የተደበቀባትን ክፍል ጭምር
አይቻለሁ። አንዳርጋቸው ይህን ቤተሰብ እንደ ስጋ ዘመዱ ያያል። እነርሱም አንዳርጋቸውን ሲያዩ በደርግ የተረሸነ
ሟች ወንድማቸውን ያስታውሳሉ።

እንግዲህ አንዳርጋቸው የመን ላይ መያዙን ስሰማ ወደ እነዚህ ሰዎች ነበር የበረርኩት። እንደደረስኩ
የግቢውን በር ደበደብኩ። አንዲት ሴት ብቅ አለች። አላውቃትም። እንግዳ ሳትሆን አትቀርም። ማንን እንደምፈልግ
ነገርኳት። የፈለግሁዋት ሴት እንደሌለች ነገረችኝ። እና የእጅ ስልኳን ሰጠችኝ። ደወልኩ። የምፈልጋት ሴት ስልኩን
አነሳች። ማን እንደሆንኩ ከነገርኳት በሁዋላ፣

“ስለ አንዳርጋቸው ሰማሽ?” ስል ጮህኩ።
“አልሰማሁም። ምን ሆነ?” ስትል እሷም ጮኸች።
“አሁኑኑ ነይ። እነግርሻለሁ…”

ከአስር ደቂቃ በሁዋላ እዚያው ከቤታቸው በራፍ ላይ ቁጭ ብለን የሰማሁትን ሁሉ ነገርኳት። ቃል
መተንፈስ እንኳ ተቸገረች። ትንፋሿ ቆሞ ድርቅ ብላ ቆየች። በመጨረሻ ግን ጥቂት ጥያቄ አዘል ቃላት ተናገረች፣

“በየመን በኩል ለምን እንደመጣ አልገባኝም? በየመንያ እንደማይጠቀም ከዚህ በፊት ነግሮኝ ነበር?”

በመቀጠል ከአንዳርጋቸው “ዘመዶች” ወደሌላው ደወልኩ። ተገናኝተን ስናወጋ ዜናውን ሰምቶ ነበር
የጠበቀኝ። ግራ ተጋብቶ ነበር። ግራ በተጋባ ስሜትም፣

“አንዳርጋቸው ከለንደን ሲነሳ ደውሎልኝ ነበር።” አለኝ። አያያዘና አከለበት፣ “…ትኬቱ በኤርትራ አየር
መንገድ ከዱባይ በቀጥታ ወደ አስመራ የተቆረጠ ነበር። ለምን በየመን በኩል እንደቀየረው አልገባኝም?”

አንዳርጋቸው ከየመን ወደ አዲሳባ መዛወሩን እስከሰማሁባት እለት የነበሩት ቀናት ለኔ እጅግ አስጨናቂ
ነበሩ። ወሬው አስመራን አዳርሶ ነበር። ፖለቲካ የማይከታተሉ ሰዎች ሳይቀሩ የአንዳርጋቸውን ስም እያነሱ ሲነጋገሩ
ሰማሁ። የኔና የአንዳርጋቸውን መቀራረብ የሚያውቁ እየደወሉ ይጠይቁኝ ነበር። አንዳርጋቸውን በፖለቲካ አቋሙ
የሚቃወሙት የኦነግ ከፍተኛ አመራር አባላት ጭምር በየመን ድርጊት ክፉኛ ተቆጥተው ነበር። የኦነግ አመራር
ከመቆጣት አልፎ የመን ላይ ዛቻ የቀላለቀለ መግለጫ አወጣ። ዳሩ ግን ማንም ምንም ማድረግ በማይችልበት
ፍጥነት አንዳርጋቸው ተላልፎ ለወያኔ ተሰጥቶ ኖሮአል። ኦሮማይ!

አንዳርጋቸው እንዴት ከወያኔ እጅ ሊገባ እንደቻለ ዛሬም ድረስ ግልፅ መረጃ የለም። የተለያዩ መላ
ምቶችን እየሰማን፣ እያነበብን ቆይተናል። አንዳርጋቸውን በቅርብ ከሚያውቁት አንዱ እንደመሆኔ እኔም ካለኝ
መረጃ በመነሳት የራሴን ግምት መውሰዴ አልቀረም። የኔን ግምት ይፋ ከማድረጌ በፊት ሌሎች የሚሉትን
ለመስማት በሚል እስካሁን ድረስ በጉዳዩ ላይ ሳልፅፍ ቆይቼ ነበር። አሳማኝ መረጃ ሳይፃፍ ወይም ሳይገለፅ ጊዜው
ስለረዘመ እነሆ! እኔም የግል አስተያየቴን ለማኖር ወሰንኩ…

ኤልያስ ክፍሌ ethiopianreview ላይ የፃፈውን አንብቤያለሁ። ግንቦት 7 የኤልያስን መረጃና ትንታኔ
በደፈናው፣ “ውሸት” ሲል ማስተባበሉንም ተከታትያለሁ። ግንቦት 7 ከማስተባበል አልፎ አንዳርጋቸው እንዴት
ሊያዝ እንደበቃ መግለፅ አለመቻሉ ግን ማስተባበሉን ጎደሎ ያደርገዋል። ያም ሆኖ የኤልያስ ክፍሌ ዘገባ ለኔ
አሳማኝ አልነበረም። በተመሳሳይ ከአንዳርጋቸው መያዝ ጋር በተያያዘ ጥቂት ወሬዎችን ተከታትያለሁ።
ከሰማሁዋቸው መካከል፣

“አንዳርጋቸው ከዱባይ አስመራ በቀጥታ የሚወስደው የኤርትራ አየር መንገድ ትኬት ነበረው። ዱባይ
ላይ የኤርትራ አይሮፕላን ስላመለጠችው የየመንን ትኬት ገዛ።” የሚለው አንዱ ነው።

ለዚህ መረጃ ክብደት ልሰጠው አልቻልኩም። አንዳርጋቸው ተጨማሪ አንድ ቀን ዱባይ በማደር
የሚቀጥለውን የኤርትራ አይሮፕላን መጠቀም እየቻለ፣ እንዴት አስተማማኝ እንዳልሆነ በሚያውቀው የመኒያ
ለመጓዝ ይወስናል? አንዳርጋቸው በየመን አየር መንገድ የተጓዘው በግማሽ ቀን ውስጥ በራሱ ውሳኔ ብቻ ከሆነ፣
የወያኔና የየመን የፀጥታ ሰዎች በዚያችው ቅፅበት አንዳርጋቸውን ለማፈን መቀናጀት ችለዋል ብሎ ማመን
ይቸግራል። የመሆን እድሉ በጣም አናሳ ነው። ለንደንም ሆነ አስመራ የሚገኙ የአንዳርጋቸው ዘመዶች የማያውቁት
አንድ ጉዳይ ያለ ይመስላል። በርግጥም አንድ ምስጢር ሊኖር እንደሚችል እጠረጥራለሁ።

ነገሩ ወዲህ ነው…

በአንድ ወቅት ግንቦት 7 ከነ ነአምን ዘለቀ እና ከአንድ የሆነ የአፋር ድርጅት ጋር ውህደት ነገር
መፈፀማቸውን በዜና ነግረውን ነበር። ከውህደቱ በሁዋላ ብዙም የተወራ ነገር ሳይኖር ነገሩ ተድበሰበሰ። ነአምን
ዘለቀ ከግንቦት 7 ጋር አብሮ ሲሰራ ስመለከት ግን አፋሮቹም ሆነ እነ ነአምን ጠቅልለው ግንቦት 7 ውስጥ ገብተዋል
የሚል ግምት ወስጄ ነበር። የአንዳርጋቸው የመያዝ ሂደት ከዚያ ሳይጀምር አልቀረም።

አንዳርጋቸው ከአፋሮቹ የፖለቲካ ድርጅት ጋር ግንኙነቱን አጥብቆ ቀጥሎ እንደነበር አውቃለሁ። ምን
እንደሚሰራ ግን ፈፅሞ ነግሮኝ አያውቅም። በመካከሉ ሆላንድ ሳለሁ ከግንቦት 7 ሰዎች በኩል የሾለከ የሚመስል
ወሬ ሰማሁ። ይህም ወሬ ለስራ ተብሎ 30 ሺህ ዶላር ተሰጥቶት ወደ የመን የተላከ አንድ አፋር የመሰወሩ ወሬ
ነበር። ወሬው በሰፊው የተሰራጨ አልነበረም። እጅግ በጣም ጠባብ በሆነ ቀዳዳ ነበር የሰማሁት። ይህ ወሬ
ሲመዘን ተራ ወሬ ሊመስል ይችላል። አፋሩ ገንዘብ መያዙ በርግጥ መረጃውን ከፍ አድርጎታል። ከገንዘቡ በላይ ግን
“የመን” የሚለው መረጃ ክብደት ነበረው። ግንቦት 7 የመን ላይ ትኩረት ማድረጉ ትልቅ መረጃ ነበር። አፋሩ
የመን-ሰንአ ሲደርስ ተሰወረ። ከዳ ወይስ ተያዘ? አይታወቅም። ከድቶም ሆነ ተይዞ ወያኔ እጅ ገብቶ ሊሆን
እንደሚችል ግን መገመት ይቻል ነበር። ይህ ከሆነ የግንቦት 7ን የተደበቀ ፍላጎት ወያኔ አውቆአል ማለት ነው።

ግንቦት 7 ምን እንደሚፈልግ ወያኔ ካወቀ፤ የግንቦት 7ን ፍላጎት ለማጥመጃ ሊጠቀምበት ይችላል። ቀላል
ጉዳይ አይደለም። ግንቦት 7 የመን ላይ ምንድነው የፈለገው? ከስደተኞች መካከል ታጋዮችን መመልመል?
የተመለመሉትን ደግሞ ወደ ተከዜ በረሃ ማሻገር? ይህን ስራ ለማከናወን ብዙ ገንዘብ ይጠይቃል። ውድ ነው።
ከሁሉም በላይ ግን ይህን ስራ ለመስራት የሚችል፣ አላማ ያለው ብቁ ሰው የመን ላይ ማግኘትን ይጠይቃል።

አፋሩ ገንዘብ ይዞ የመን ላይ ከተሰወረ በሁዋላ አንዳርጋቸው ተስፋ ቆርጦ ጉዳዩን ይተወዋል ተብሎ
አይገመትም። እንደገና ይሞክራል። ወያኔዎች በዚህ በአንዳርጋቸው ዳግማዊ ሙከራ ጊዜ የራሳቸውን ሰው የመን
ላይ አስቀምጠው አንዳርጋቸውን እንዲገናኘው አድርገው ይሆን? አንዳርጋቸው በረጅም ሂደት ወያኔዎች
ያዘጋጁለትን ሰው እንደራሱ ሰው በማመን ለግንቦት 7 አባልነት በምስጢር መልምሎት ይሆን? እና በረጅም ጊዜ
ሂደት አንዳርጋቸው ወያኔዎች ባዘጋጁለት ወጥመድ ውስጥ ሰተት ብሎ ገብቶላቸው ይሆን? ማለትም አንዳርጋቸው
እነዚያ አባላቱን ለማነጋገር፣ አሊያም ታጋዮቹን ወደ ተከዜ ለማሸጋገር እንዲቻል አንዳንድ ጉዳዮችን ለመፈፀም
በምስጢር የመን ገብቶ ለመውጣት ሞክሮ ይሆን?

ጥያቄዎቹ “አንዳርጋቸው እንዴት ተያዘ?” ለሚለው ጥያቄ ፍንጭ ሰጪ ሊሆኑ ይችላሉ። ቀጥተኛ መረጃ
ያለው አካል የተፈፀመውን በዝርዝር እስካልነገረን ድረስ ከምናውቀው በመነሳት ለመገመት እንገደዳለን።

ከዚህ ሁሉ በሁዋላ፣ “ወያኔዎች አንዳርጋቸውን ይዘው በማሰራቸው አተረፉ ወይስ ከሰሩ?” የሚል ጥያቄ
ይነሳል። የወያኔ ሰዎች “አተረፍን” እያሉ ነው። ማትረፍና መክሰራቸውን ለማየት በርግጥ ጥቂት ጊዜ መጠበቅ
ያስፈልግ ይሆናል። “አትርፈናል” ባዮች ከበሮ ሲደልቁ ሰምተናል። በአንዳርጋቸው መያዝ ቆሽቱ የደበነ ወገን፣ ነገ
በቁጣ ምን ሊፈፅም እንደሚችል አለመገመት የፖለቲካ የዋህነት ነው። እነ በቀለ ገርባ፣ እነ እስክንድር ነጋ፣ እነ
ኦልባና ሌሊሳ፣ እነ ኢንጂነር መስፍን አበበ (ራሶ)፣ እነ ጫልቱ ታከለ፣ እነ ኢብራሂም ሱልጣን፣ እነ ሰይድ አሊ፣ እነ
ፊፈን ጫላ፣ እነ ኮሎኔል ኦላኒ ጃሉ፣ እነ ውብሸት ታዬ፣ ዛሬም ድረስ እስርቤት ናቸው። አንዳርጋቸው ፅጌ
ተጨምሮአል። ይህን ፅሁፍ እየጻፍኩ ሳለም በርካታ ነፃነት ጠያቂዎች እየታፈኑ ወደ እስር ቤት በመጓዝ ላይ ነበሩ።
እስርቤት የተወረወሩትን ዜጎች በቀን 24 ሰአት የሚያስታውስ በሚሊዮን የሚቆጠር ዜጋ በመላ ኢትዮጵያ አለ።

በደል ሲበዛ ወደ በቀል ይለወጣል። ብዙውን ጊዜ ተበዳዮች ጉልበት ሲያገኙ የማመዛዘን ችሎታቸውን
ያጣሉ። በቀል ከመጣ ከደሙ ንፁህ የሆነውን ከተጠቃሚው መለየት ሳይቻል ጊሎቲኑ ከፊቱ ያገኘውን ሊበላ
እንደሚችል ከታሪክ በተደጋጋሚ አይተናል። ወያኔ አንዳርጋቸውና መስፍን አበበን በመሳሰሉ ታጋዮች ላይ
እየፈፀመ ባለው የማፈን ድርጊት ከህዝቡ መራር ቂም በማትረፍ ላይ ነው። ጭፍን ደጋፊዎቹ አደጋ ላይ
እንዲወድቁም አጋልጦ እየሰጣቸው ነው። በመሆኑም ወያኔ አትራፊ ስለመሆኑ ማረጋገጥ አይችልም።

የፅጌ ልጅ – አንዳርጋቸው ከጠላቶቹ እጅ ላይ ወድቆአል። በወያኔ ቴሌቪዥን ላይ ቀርቦም ጥቂት ቃላትን
ተናግሮአል። አንዳርጋቸው በጨካኝ ጠላቶቹ እጅ ላይ ወድቆ ሳለ የተናገራቸውን ቃላት በቀጥታ መውሰድ ወይም
ንግግሩን እንደ መረጃ ተጠቅሞ በዚያ ላይ አስተያየት መስጠት ተገቢ አለመሆኑን እረዳለሁ። ያም ሆኖ
አንዳርጋቸው በንግግሩ፣ “እኔን ተክቶ በረሃ የሚወርድ ሰው ማግኘት ይቸግር ይሆናል” አይነት አባባል መጠቀሙ
በተዘዋዋሪ የትግል ጥሪ ይመስለኛል። መስማት የሚፈልግ ካለ ይህን ሊሰማ ይችላል…

ርግጥ ነው አንዳርጋቸው ከተያዘ በሁዋላ በመላ አለም የሚገኙ “የአንድነት ሃይሎች” በቁጣ የተቃውሞ
ሰልፎችን አካሂደዋል። “አንዳርጋቸው ነኝ!” የሚል መፈክር ይዘውም ታይተዋል። “ሁላችንም አንዳርጋቸው ነን!”
የሚለው መፈክር ለአንዳርጋቸው ተገልብጦ ስድብ እንዳይሆንበት ግን እሰጋለሁ። “አንዳርጋቸው ነኝ!” ለማለት
ቢያንስ አንዳርጋቸው የሞከረውን ለመሞከር ቁርጠኛነትን ማሳየት ይጠይቃል። “ሁላችንም አንዳርጋቸው ነን!”
የሚለው አባባል በአፍ ብቻ ተንጠልጥሎ ከቀረ፣ እንደተለመደው የአንድ ሰሞን የዳያስፖራ ጫጫታ ሆኖ እንደ
ቀዳሚዎቹ መፈክሮች ይህም ከተረሳ ለአንዳርጋቸው ስድብ እንጂ ክብር ሊሆነው አይችልም።

የቅዳሜ ማስታወሻ – December 12, 2014 – Tesfaye Gebreab (Gadaa) – Email: ttgebreab@gmail.com

ግንቦቶች ራሳቸውን መጠየቅ ያለባቸው

By ግርማ ካሳ

image

የተባበሩት መንግስታት አጣሪ ቡድን በኤርትራ ላይ ይፋ ያደረገዉን ሪፖርት በተመረኮዘ በቅርቡ በሰጠሁት አስተያየት ዙሪያና የመለስ ቱሩፋቶች የሚለዉን መጽፍ የጻፈ፣ እስከ ቅርብ ጊዜ የሕወሃት/ኢሕአዴግ ከፍተኛ አመራር የነበረ አቶ ኤርሚያ ፣ በርካታ ጊዜያት በኢሳት መቅረቡን ጠቅሼ፣ “ኢሳት የኤርሚያስ ሾው ሆነ እንዴ ?” የሚል ጥያቄ በማንሳቴ፣ ከወትሮ በተለየ ሁኔታ በርካታ አስተያየቶች ቀርበዉልኛል። ስለኢሳትና ስለ አቶ ኤርምያስ ወደፊት የአቶ ኤርሚይስን መጽሃፍ ካነበብኩ በኋላ እመለስበታለሁ። አሁን ስለግንቦት ስብት ትንሽ ልበል።
ግንቦት ሰባትን የመሰረቱ ወገኖች ለምን ግንቦት ሰባትን እንደመሰረቱ አውቃለሁ። በወያኔ ትልቅ ግፍ የተፈጸመባቸውና የተናደዱ ፖለቲከኞች ናቸው። አቶ አንዳርጋቸው ጸጌ፣ ዝዋይ በዘጠና ሰባት ታስሮ በነበረ ጊዜ በሰደፍ አይኑን መተዉታል ፣ እሰከአሁን ድረስ አይኑ ላይ ችግር አለበት። በሚገባ ይገባኝል ንዴቱና ብሰጭቱ !!!!!!!!

ነገር ግን ንዴትና ብስጭት ብቻ አገርን ነጻ አያወጣም። በየአዲስ አመቱ ንግግር ማድረግ፣ በየሰብሰባው ትያትራዊ በሆነ መንገድ ሕዝቡ ጠንቅቆ የሚያወቀዉን የወያኔን ሐጢያት እየደጋገሙ መናገር ለዉጥ አያመጣም። ነገር ግን ሁሉንም ያገናዘበ፣ ዉጤታማነቱ በየጊዜው የሚፈተሽ፣ የሚጠቅም ስትራቴጂ ያስፈልጋል።
የግንቦት ሰባት ንቅናቄ ብዙ የሰራቸውና ያስመዘገባቸው ዉጤቶች አሉ። ለነጻነትና ለፍትህ በሚደረገው ትግል ዉስጥ ትልቅ ሚና ሊጫወት ይችላል ብዬ አምናለሁ። ነገር ግን ከሻእቢያ ጋር ያለውን ግንኙነት መመርመር አለበት የሚል ጠንክራ እምነት አለኝ። ግንቦት ሰባትን ስተች፣ በድርጅቱ አባላትና ደጋፊዎች መካከል ጤናማ የሆነ ዉይይት እንዲኖር ለማበረታታትም ነው። አባላትና ደጋፊዎች በጭፍን መከተል አቁመው መሰረታዊ ጥያቄዎችን እንዲጠይቁ ነው። ድርጅቱ ከተሳሳተ መንገዱ ተምልሶ ጥቅም በሚያመጥብት መንገድ እንዲሰማራ ግፊት ለማድረግ ነው።

እስቲ ትንሽ ከሃያ ሶስት አመታት በፊት ወደነበረው ሁኔታ ልመልሳችሁ። ሻእቢያ መጀመሪያ ሰሞን ከኢሕአፓ ጋር ወዳጅ ነበር። ኢሕአፓ አገር ቀፍ በመሆኑ፣ ፊቱን ወደ ሕወሃት አዞረ። ሕውሃትን አጠናከረ። ሕወሃት ትግራይን በተቆጣጠረ ጊዜ ወደ ደቡብ መዝለቅ አልቻለም። ስለዚህ እነ ታምራት ላይኔ ብቅ አሉ። እነ ታምራት፣ ፊት ፊት እየቀደሙ ጎንደሬዉን፣ ወሎዬዉን እየቀሰቀሱ ሕወሃት ያለ ምንም ችግር ወደ መሐል አገር እንዲገባ አደረጉ። ከዚያ አዲስ አበባ ሲገባ፣ ሚሊተሪዉን የያዙት ሕውሃቶች ስለነበሩ፣ እነ ታምራትን ወደጎን አድርገው፣ በቀላሉ ስልጣን ላይ ተቆናጠጡ። ይኸው እስከዛሬ ድረስ የነታምራት ቡድን የሕውሃት እንደራሴን አሽከር ሆኖ፣ እንወክለዋለን የሚሉት “አማራው” እንኳን ከኦሮሚያ፣ ቤንሻንጉል አገርህ አይደለም እየተባለ በኦህዴድ/ኢሕአዴግ ካድሬዎች በግፍ ሲፈናቀል፣ የጎንደር ለምለም ግዛት የነበረው ወልቃይት ጠገዴ ወደ ትግራይ እንዲዞር ሲደረግ፣ ከጎንደር መሬት ተቆርሶ ለሱዳን ሲሰጥ ምንም ማድረግ ያልቻለ ቡድን ሆኗል።

አሁንም ተመሳሳይ ሁኔታ ነው እየተፈፀመ ያለው። ሻእቢያ በአገር አቀፍ ድርጅቶች እመኔታ የለውም። ሥለዚህ የራሱን የሚያምንበትን ድርጅትን አጠናከረ። ደሚትን። ግንቦት ሰባትም ከደሚት ጋር እንዲሰራ ሻእቢያዎች ሲጠይቁ (ምናልባትም ሲያዙ) ግንቦት ሰባት ለመስራት ተሰማማ። ልክ እነ ታምራት ለህወሃት እንደሆኑት፣ ግንቦት ሰባት ደግሞ ለደምሚት ለመሆን ተዘጋጀ። ይኸው የሻእቢያ ልጅ የሆነውን ደሚት እየካቡልን ነው።

እስቲ አንድ ሴንሪዮ እንመልከት።እንበል ጦርነት ተከፍቶ፣ ግንቦት ሰባትና ደሚት አሸንፈው አዲስ አበባ ገቡ። ሚሊተሪዉን የያዘው ደሚት እንደመሆኑ፣ ዶር ብርሃኑ አዲሱ ታምራት ላይኔ ሆነው፣ የደሚቱ መሪ ደግሞ አዲሱ መለስ ዜናዊ እንደሚሆኑ መቼም መገመት አያቅተንም። ግንቦት ስባቶች እኛ ሥልጣን ለመያዝ አይደለም፣ ወያኔ ከወደቀ በኋላ አገር አቀፍ ኮንፈራንስ ይደርጋል ይላሉ። ነገር ግን ሕወሃት ያኔ እነ በየነ ጰጥሮስን፣ እነ ሌንጮን ሰብስቦ ኮንፍራንስ እንዳደረገው፣ በደሚትና በግንቦቶች የሚደረገው ኮንፈራንስ፣ የይስሙላ ነው የሚሆነው። ጠመንጃ ያለው ኃይል ነው የሚገዛው። እርሱም ደሚት። በመሆኑም የግንቦት ሰባት ዘመቻ፣ በርግጠኝነት ኢትዮጵያን ነፃ ለማውጣት ሳይሆን፣ ቀዳሚዉን ሕውሃት በዳግማዊ ሕውሃት በመተካት፣ በቅድመ ባድመ አመታት እንደነበረው፣ ኢትዮጵያ በእጅ አዙር በሻእቢያ እንድተገዛ የሚያደርግ ነው። አንድ በሉ።

ሌላው እነ ኦነግ፣ የአርበኞች ግንባር የመሳሰሉት ሲዳከሙ ደሚት ለምን ሊጠናከር እንደቻለ እንድንመረመር እፈልጋለሁ። እስቲ አስቡት፣ በትግራይ ሕውሃት ብዙ ግፍ ቢፈጸምም፣ በመሀል አገር በተለይም በኦሮሚያ እንደተፈጸመው አይሆንም። ታዲያ ኦነግ፣ የአርበኞች ግንባር ብዙ ወታደር ሳይኖራቸው፣ እንዴ ደሚት ብዙ ወታደሮች ሊኖረው ቻለ ? መልሱ ቀላል ነው። ሻእቢያ ጠንካራ ግንቦት ስባት፣ ጠንካራ የአርበኞች ግንባር እንዲኖር አይፈልግም። ሻእቢያ፣ ደሚት የበላይነቱን የያዘበት ኃይል እንዲኖር ነው የሚፈልገው።(ያኔ ሕወኃት የበላይ ሆኖ እንደነበረው) ሁለት በሉ።

በሶስተኛነት የማነሳው የግንቦት ስባት የፖለቲካው አመራር ምን ያህል በኤርትራ ያለውን ተጨባጭ ሁኔታ ያውቅል በሚለው ላይ ነው። ግንቦት ሰባት ለአራተኛ ጊዜ ወታደርች እንዳስመረቀ አንብበናል።(ከዚህ በፊት የተመረቁት የት እንዳሉ ባናውቅም) የግንቦት ስባት አመራሮች ምን ያህል እርግጠኛ ናቸው ስልጠና መደረጉን ? በድህረ ገጾች የምናየው ፣ በኢሳት የምንሰማው የለየለት የሻዕቢያ ድራማ ስላለመሆኑ ምን ማረጋገጫ አላቸው ? ልሳሳት እችላለሁ፣ በስፋራው ሄዶ መረጃ ሰብስቦ የመጣ ከፍተኛ የአመራር አባል አለ ብዬ አላስብም። ምናልባት ዶር ብርሃኑ ነጋ እራሳቸው ቢያንስ አለ የሚሉትን ጦር ለማበረታት፣ ለተመረቅት የምስክር ወረቀት ለመስጠት፣ ያለዉን ሁኔታ በአይናቸው አይተው ደጋፊዎች ጥያቄ በሚያቀርቡበት ጊዜ በድፍረት ለመናገር ይረዳቸው ዘንድ ለምንስ ወደ ኤርትራ አይጓዙም ? ሌላው ኢትዮጵያዊ ወደ አስመራ ሄዶ እንዲዋጋ ጥሪ እያቀረብን፣ እኛ ግን አካባቢው ለመድረስ የምንፈራ ከሆነ እኛ የምንመራው ድርጅትስ እንዴት ተቀባይነት ሊኖረው ይችላል ? በሞራል አንፃርስ ትክክል ነው ወይ ?
በግሌ ለመብቱና ለነጻነቱ ፣ ለአገሩ ሲል ነፍጥ የሚያነሳ ሰው በጣም አከብራለሁ። ነገር ግን እርሱ ቤቱ ሶፋ ላይ ቁጭ ብሎ፣ የድሃው ልጅ ሕይወቱን እንዲገብር የሚያዝ መሪ ግን አይመቸኝም። ለአቶ አንዳርጋቸው አክክብሮት ደካማ አመራር ነው። አራት በሉ።

ግንቦት ሰባቶች እንዲሁ ይፎክራሉ እንጂ ጦረኞች አይደሉም። አንደኛ ጦረኛ ሰው ብዙ አያወራም። የጦረኛ ሰው ቋንቋዉ የጥይት ድምጽ እንጂ ቴሌዝዥን እና ኢንተርኔት አይደለም። ዶር ብርሃኑ የአፍ ጀግና ግን የባሩድ ሽታ የሚፈሩ ናቸው። እንደኔ ካሉ በፌስ ቡክና በድህረ ገጽ ከሚለቀልቁ በምንም አይለዩም። ለዚህም ነው ዉጤት አላመጣችሁበትና፣ አያምርባችሁምና፣ ከሻእቢያ ጋር የምታደርጉትን ዳንኪራ አቁሙና፣ ጎበዝ በሆናችሁበት፣ በተካናችሁት፣ ዉጤት ልታመጡበት በምትቹሉት ሥራ ተጠመዱ የምላቸው። እስቲ አስቡት፣ አሁን ማራዶና ተከላካይ ቢሆን ? የነ ዶር ብርሃኑም ነገር እንደዚያ ነው።
እንግዲህ የሚሰሙ ከሆነ ምክሬን በድጋሚ እለግሳለሁ። ከሻእቢያ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በጥሰው፣ ከሌሎች ኢትዮጵያዊ ድርጅቶችና ቡድኖች ጋር አብረው መስራት ቢጀመሩ ጥሩ ነው። ሻእቢያ ከኢትዮጵያ ፖለቲካ ዉስጥ መዉጣት አለበት። ሻእቢያ ለኢትዮጵያ ብቻ ሳይሆን ለኤርትራ ህዝብ፣ ለምስራቅ አፍሪካ በሙሉ መወገድ ያለበት ነቀርሳ ነው። በዉጭ ያለነው እኛ ኢትዮጵያዉያን እንዳንስማማ ያደረገን፣ በጉዳያችን ገብቶ የከፋፈለን ሻእቢያ ነው። ከሻእብያ ጋር በመስራታቸው ቅንጣት ያህል በወያኔ አገዛዝ ላይ ያስመዘገቡት ድል የለም። በአንጻሩ ወያኔን ሊያንበረክክ የሚችል የተቃዋሚዎች አንድነት እንዳይኖር ግን፣ ሻእቢያ አንዱና ትልቁ ምክንያት ሆኗል።
አውቃለሁ፤ ቁስል ያለበት ሰው ቁስሉ ሲነካ ያመዋል። ግንቦቶችም በጻፍኩት ነገር ሊናደዱ ይችላሉ። ነገር ግን የማታ ማታ እዉነቱን ስለነገርናቸው ያመሰግኑናል ብዬ አሰባለሁ።

Ginbot7 TO: The United Nations Security Council Sanctions Committee

Ginbot7

FOR IMMEDIATE RELEASE

MEMORANDUM

TO: The United Nations Security Council Sanctions Committee

FROM: Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy.

DATE: October 27, 2014

SUBJECT: Response to References made about Ginbot 7 in the Report of the Monitoring Group of Somalia and Eritrea (here after SEMG), Pursuant to UN Security Council Resolution 2111 (2013).

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy expresses its high regards to The United Nations Security Council, and would like to use this opportunity and bring to the attention its reservations regarding some references made about it in SEMG report of October 13, 2014.

 

1. The SEMG report states that “Ginbot 7 is a banned opposition group”. We would like to call the attention of the International Community to the infamous “Anti-Terrorism Proclamation” promulgated by the TPLF/EPRDF regime of Ethiopia with the aim of stifling political dissent. The dictatorial regime has used this proclamation as an instrument to label and criminalize Ginbot 7, as well as other political opposition organizations, human rights advocacy groups, civil society, journalists and bloggers inside and outside of Ethiopia.

 

2. Let alone the claim in the report that Ginbot 7 was established in 2005, which is categorically false, even the so-called Anti-Terrorism Proclamation was not promulgated until 2009.

 

Ginbot 7 was formed in 2008 after few members among its leadership spent almost two years in prison in the aftermath of the ill-fated election of May 15, 2005. As well known by the International community, the regime overturned the election results that clearly showed the opposition party Coalition for Unity and Democracy (CUD) has won the majority throughout the country. This is a fact corroborated by international election observes such as the European Union’s Election Monitoring Group that was present in Ethiopia to observe the election in 2005. Those who formed Ginbot7, then leaders of the CUD, were among the leaders thrown in prison on trumped up charges.

 

Ginbot 7 was formed as a political movement in order to advance justice, freedom, and liberal democracy in Ethiopia. Ginbot 7 believes that no meaningful and genuinely competitive elections can take place in the country due to the prevailing and ever worsening egregious human rights violations, the closing of political space, the harassment and persecution of members of the legal and peaceful political opposition. Furthermore, an entrenched minority ethnocratic dictatorship in Ethiopia has determined to perpetuate its hold on power by all and any means necessary.

 

3. SEMG’s claim in the report that Ginbot 7 was established by “Amhara elites” is grossly erroneous given the ethno-religious mix of its leadership and membership. The report’s characterization of Ginbot 7 as an organization established by “Amhara elites” is not only factually inaccurate, but a clear indication of the bias of the report. It seems like SEMG has bought lock, stock and barrel the dictatorial regime’s fabricated story of Ethiopian politics as an entirely ethnic based phenomena.

The SEMG could have easily established the facts by taking a cursory look at Ginbot 7′s website rather than unquestioningly accepting the regime’s characterization with regard to Ginbot 7′s multi ethnic membership and leadership, its organizational principle and its well established position on ethnic based politics in Ethiopia. No effort seems to have been made by the SEMG to balance its report by counterchecking its claims from Ginbot 7 or other sources instead of recycling the minority regime’s long standing targeting and demonization of the Amharas, the second largest ethnic group in Ethiopia.

 

4. The SEMG, despite its familiarity with political conditions in the Horn of Africa, fails to realize what is very obvious to all regarding the TPLF/EPRDF regime’s agitation, use of threat, torture and at times bribery when presenting helpless prisoners under its custody to echo unfounded guilt they are coerced to rehearse for interviews and media presentations. Hence, presenting forced confessions and unreliable information from such prisoners as evidence is beyond comprehension.

 

5. The SEMG’s claim to have retrieved information from an alleged Ginbot 7 fighter captured in Gonder is no different from what is explained above.

 

6. SEMG’s reference in its report to weapons’ serial numbers to suggest the source of certain weapons as being from Eritrea, clearly neglects the fact that numerous prisoners of war, weapons and ammunitions have exchanged hands between Ethiopian and Eritrean forces during their numerous wars.

7. Needless to say that the SEMG has been manipulated to construe that Ginbot 7 needs to extend its recruitment to the southern tip of Africa, while what Ginbot 7 objectively faces is the capacity to accommodate the tens of thousands forcing their ways into its fold from amongst the millions who support it. These are Ethiopians from very diverse backgrounds seeking a genuinely liberal democratic and just order, freedom and equality which have been denied to them by the brutal dictatorial regime of the TPLF/EPRDF.

 

8. It is unfortunate to note that the SEMG has been misguided to misrepresent Ginbot 7’s prevailing organizational reality that clearly demarcates boundary between its own political bodies from that of other organizations that may have opted to attain their objectives by any other means they deem appropriate.

9. Ginbot 7 found the claim in the report regarding persons SEMG suggests were received by Andargachew Tsege upon their arrival in Asmara and who have “joined a group of 30 to 60 Ginbot 7 fighters at Harena Military Camp” comical, simply because the arithmetic percentile between 30 and 60 is 100% and hence too large a difference for any wrong guessing.

 

10. The SEMG clearly states in its report that it was unable to verify the claims of the alleged Ginbot 7 fighters, which begs the question, then, as to why the SEMG had to dwell in its defamatory claims and tarnish the image of Ginbot 7.

11. The same can be said about SEMG’s statement in its report regarding its inability to assess the extent of this unsubstantiated support as compared with Asmara’s support of Ginbot 7 in the past.

 

12. The SEMG seems to be deliberately overlooking or otherwise incognizant of TPLF/EPRDF regime’s well recorded expertise in passport, travel document, and other forms of forgeries going back to its days as a guerrilla force. Had this not been the case, understanding the nature of documents presented to it by the regime’s security officials, should not have been beyond the comprehension of the SEMG.

The allegations by SEMG may be well calculated and deliberate distortions aimed at upholding the sanctions imposed on Eritrea. However, we fail to comprehend why Ginbot 7, or the Ethiopian people for whose rights our organization is struggling for, is interjected in these maneuvers.

 

Ginbot 7, however, would like to use this opportunity to assure all concerned, including the United Nation’s Security Council, that it is ready to give freely and candidly tangible explanations related to its mission and the achievements in the process of registering its just struggle.

 

Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy would like to respectfully conclude its MEMORANDUM by strongly affirming that it stands ready and willing to cooperate with the International Community, in good faith, and contribute everything within its capacity for sustainable regional peace and stability in the Horn of Africa.

We look forward to your timely reply.

አሸባሪ ብዕሮች

By Kinfu Assefa

image

ይህች አጭር ጽሁፍ የተወሰደችው በአውስትራሊያ ከምትታተም “አሻራ” ከተሰኘች መጽሄት ልዩ እትም ላይ ነው።

የፈረንሳዩ አንባገነን ገዥ የነበረው ናፖሊዮን ቦናፓርት በአንድ ወቅት ስለ ነጻ ፕሬስ ሲናገር “ከአንድ ሺህ ሻምላዎች ይልቅ አራት ጋዜጦች የበለጠ መፈራት አለባቸው።” ነበር ያለው።

አንባገነኖች ፕሬስን ይፈራሉ። ይጠላሉም። የህዝብ መሰረት የሌላቸው፤ በራሳቸው የማይተማመኑ ሁሉ ነጻ ሃሳብን ይጠላሉ። ነፍጥን ብቻ ተማምነው በሕዝብ ጫንቃ ላይ የሚቀመጡ፤ እንደምን ነጻ አመለካከትን ሊቀበሉ ይችላሉ? ፍጹም አንባገነናዊነት በሰፈነባቸው እንደ ኢትዮጵያ ባሉ ሀገሮች፤ ህግ አውጭው ህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ የለም። ይህንን ቁጥጥር በጥቂቱም ቢሆን ተክቶ ይሰራ የነበረው ነጻው ፕሬስ ነው። ከዚህም አልፎ ሕዝቡ መብቱን እንዲያውቅና መብቱንም እንዲያስከብር ብዙ ሰርቷል-ፕሬሱ። ሙስናን አጋልጧል፣ እንደ እንባ ጠባቂም እየሆነ የህዝብን በደልም ይፋ አድርጓል። ይህን የተቀደሰ ተግባር ማከናወን እንደወንጀል፤ ጠንከር ሲል ደግሞ እንደ ሽብርተኝነት የሚቆጠርበት ሃገር ሆናለች የዛሬይቱ ኢትዮጵያ።

መብትን ማወቅ እና ማሳወቅ፤ ‘ህዝብ ለጦርነት እንዲነሳ ማድረግ፤ ወይንም በስራዓቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር ነው’ ተብሎ ከተተረጎመ ደግሞ ጋዜጠኛን በአሸባሪነት መፈረጁ ብዙ ሊደንቀን አይገባም።

ኢትዮጵያ ላለፉት አስርት-አመታት ጋዜጠኞችን በማሰር ከአፍሪካ በቁጥር አንደኛ ደረጃ ላይ የነበረች ሃገር ናት። አሁን ይህንን ደረጃዋን ለቃለች። እድገትና ትራንስፎርሜሽኑን ተከትሎ ከመጡት ለውጦች አንደኛው መሆኑ ነው። ኢትዮጵያ የአንደኝነት ደረጃዋን ያጣችው ታዲያ ትራንስፎርሜሽኑ ይዞት በመጣው መሻሻል አይደለም። ነጻ ፕሬሱ ከሃገሪቱ እንዲጠፋ በተደረገ ሁለገብ ጦርነት እንጂ። አብዛኛው ጋዜጠኛ ተሰድዷል፣ ጥቂቶቹ ታስረዋል፣ አንዳንዶቹም አቅማቸው ተሟጦ አልቆ፤ ዝም ብለው እንዲቀመጡ ተደርገዋል። ለነጋሪ የተረፉትንም እስከዛሬዋ እለት ድረስ እያሳደዷቸው ይገኛሉ።

ከጅምሩ በፕሬሱ ላይ የተከፈተው የገዥው ፓርቲ ውግያ ቀላል አልነበረም። ፕሬሱ ግን እለት ተዕለት የሚያርፍበትን የአንባገነኖች ጡጫ ሁሉ ችሎ ብዙ ተጉዟል። እየተንገዳገደ፤ እየወደቀና እየተነሳ የህዝቡን የህሊና ንቃት እንዲሰፋ ከማድረጉም ባሻገር በኢትዮጵያ የማንበብ ባህል እንዲዳብር ነጻው ፕሬስ ተግቶ ሰርቷል። የህትመት ዋጋ እስከ 500% እንዲጨምር ቢደረግም ፕሬሱ አልቆመም ነበር። ጋዜጠኞች እንደጥጃ እየታሰሩ፣ እየተደበደቡ፣ እየተሰቃዩም ስራቸውን ላለማቋረጥ መትጋታቸውን አላቆሙም። በካድሬ ዳኞች ፍርደ-ገምድል ፍትህ ሲሰጣቸው፤ ያለ አግባብ በእስርና በገንዘብ ሲቀጡም ሰራቸውን አላቋረጡም…

የአሜሪካው ፍሪደም ሃውስ በተከታታይ ባወጣቸው ዘገባዎች ኢትዮጵያን ፕሬስ (Status: NOT FREE) “ነጻ ያልሆነች” ሃገር ሲል ፈርጇል። የፕሬስ አዋጁንም ፍጹም አፋኝ ሲል ይከሳል። የፈረንሳዩ ሪፖርተርስ ዊዝ አውት ቦርደርስ፣ የኒውዮርኩ ሲ.ፒ.ጄ. እና የብራስልሱ አይ.ኤፍ.ጄ. በሽብር ክስ የተያዙ የጋዜጠኖችን ሰነድ እያከታተሉ አሳፋሪነቱን ቢገልጹም አፍ እንጂ ጆሮ ከሌለው ስርዓት ያገኙት የስድብ ምላሽ ብቻ ነው። አምነስቲ ኢንተርናሽናል እና ሂዩማን ራይትስ ዋችም አፈናውን ይፋ ማድረጉን ተያይዘውታል። ከገዥው ፓርቲ የሚያገኙት ምላሽ “የኒዮ ሊበራል” አቀንቃኞች የሚል ስድብ እና ዛቻ ብቻ ነው።

ከምርጫ 97 ነኋላ ግን የህወሃት እድገት እና ትራንስፎርሜሽን፤ ጫን ያለ ነገር ይዞ ብቅ አለ።

ሽብርተኝነት!

ከዚህ በኋላ ጋዜጠኛ በህገ-መንግስት ሳይሆን፤ ህጉን በሚጻረረው አዋጅ መዳኘት እንዳለበት ተነገረ። ስርዓቱም በባሩድ ሳይሆን ይልቁንም በብእር ጫፍ እንደሚሸበር አረጋገጠ።

ይህ የሽብርተኝነት አዋጅ ቃል በቃል የተቀዳው ከአሜሪካ እና ከእንግሊዝ መንግስታት ሰነድ መሆኑን ሃይለማርያም ደሳለኝ ለቢቢሲ ሲናገሩ ተደምጠዋል። ድንቅ ነው። ሰውየው ግን ምን እየተናገሩ እንደሆን የሚያውቁት አይመስልም። በዚህች በሙት መንፈስ የምትመራ ሃገር ሌላም ብዙ እንግዳ ነገር እንሰማለን። የቡሽ አስተዳደር ከቶኒ ብሌየር ጋር አልቃይዳ የተባለውን አደገኛ ሽብርተኛ ለማጥፋት የነደፉት ይህ ሰነድ ዛሬ ኢትዮጵያ ውስጥ ጋዜጠኞችን ለማጥፋት እየተጠቀሙበት እንደሆነ ነው የሚነግሩን። የፈረንጆቹ ሽብርተኝነት (terrorism) ሲተረጎም፤ “በሃይማኖት ወይንም በርዕዮተአለም ጥላ ስር ተደራጅቶ አመጽን የማድረግ ተግባር” እንደሆነ ይነግረገናል።

በሽብርተኝነት ተወንጅለው በየእስር ቤቱ የተጣሉት የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች፤ የትኛውን ርዕዮተ-አለም ወይንም ሃይማኖት ተንተርሰው አመጽ እንደፈጠሩ፣ የትኛውን አውሮፕላን እንዳስጠለፉ፣ የትኛውን ህንጻ እንዳፈረሱ፣ የትኛውን ንጹህ ዜጋ እንደገደሉ አልተነገረንም።

እርግጥ ነው። የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እየተቹ ይጽፋሉ። ትችቱ ታድያ ለውጡ ላይ አይደለም። የለውጡ አቅጣጫ ላይ እንጂ። አቅጣጫው ትክክለኛ መስመር መያዝ እና አለመያዙን መተቸት “ወንጀል ነው” ሲባል ለቀረው አለም አዲስ ነገር ሊሆን ይችላል። ከዚያ የባሰም አለ። ገዢውን ፓርቲ መተቸት እና ስለ ለውጥ አስፈላጊነት መጻፍ በሽብርተኛነት ያስከሰሰ ወንጀል ሆኖ ሰማን። አስቂኙ ነገር፤ አዋጁ ለኦሳማ ቢን ላደን ሽብር በምእራባውያን ሀገሮች የረቀቀ የጸረ-ሽብር ህግ መሆኑ ነው።

ጋዜጠኞች በሽብርተኝነት ሲፈረጁ ነው ነጻው ፕሬስ በኢትዮጵያ አፈር የለበሰው። ይህ የመጨረሻ ጥይታቸው መሆኑ ነው። አለማቀፍ የጋዜጠኞች ተሟጋች ተቋማት ሳይቀሩ ተስፋ የቆረጡ እስኪመስል ድረድ በዘንድሮ አመታዊ ዘገባቸው የኢትዮጵያን ጉዳይ ችላ ብለውታል። እነዚህ ተቋማት በየአመቱ ስለኢትዮጵያ ፕሬስ ሁኔታ የሚያወጧቸው ዘገባዎች የሚዘገንኑ ነበሩ። ወያኔን የማይማር፣ የደነዘዘ እና የማይለወጥ ስርዓት አድረገው ስላዩት ችላ ያሉት ይመስላል። ሃያ አመት የማይሰማ፣ ያሃ አመት የማይሻሻል፣ ሃያ አመት የማይማር ስርዓት… ውሃ ቢወቅጡት እንቦጭ ሆነባቸው።

በምርጫ 97 ሰሞን በርካታ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች ቃሊቲ ተወርውረው ነበር። በጉዳዩ ላይ የአምነስቲ ኢንተርናሽናል ዲያሬክተር ከነበሩት ዶ/ር ማርቲን ሂል ጋር ስናወራ አንድ ጥያቄ አነሱልኝ።

“ለመሆኑ ሰርካለም ፋሲል ላይ ለምን እንዲህ ጨከኑባት? ” የሚል ነበር የማርቲን ጥያቄ። እኝህ ታላቅ ሰው ይህን ጥያቄ ለምን እንዳነሱልኝ አሁን ነው የተገለጠልኝ።

የሰርካለም ፋሲልን ጉዳይ ማንሳቱ የኢትዮጵያን ፕሬስ የሰቆቃ ጉዞ በከፊልም ቢሆን ይገልጸዋል።

ሰርካለምን ከባለቤትዋ እስክንድር ነጋ ጋር አፍነው ወደ ቃሊቲ ሲወስዷት ነብሰ-ጡር ነበረች። የመውለጃዋ ቀን ሲደርስም ከእስር አልለቀቅዋትም። በምጥ ስቃይ፣ ነብስ ውጭ፤ነብስ ግቢ ሁኔታ ውስጥ ሆና እንኳን አሳሪዎችዋ ርህራሄ አላሳዩዋትም ነበር። በመጨረሻ እዚያው ቃሊቲ እስር ቤጥ ናፍቆትን ተገላገለች። በዚያ የጭንቅ ወቅት የሚይዘውን እና የሚጨብጠውን ያጣ ስርዓት ምን እያደረገ እንደነበር እንኳን በውል አየውቀውም። “የመንግስት ጠላት” የሚል ታፔላ ተለጥፎለት የሚንቀሳቀስ ጋዜጠኛ፤ ሊወድቅ ከሚንገዳገድ ስርዓት ከዚህም በላይ ሊደረግበት እንደሚችል ለማስረዳት ሞከርኩ።

ነብሰ-ጡርዋ ሰርካለም የተከሰሰችው ህገ-መንግስታዊ ስርዓቱን በሃይል ለመናድ እና ለማፍረስ፣ ጥላቻን የምታስፋፋ፣ ጥርጣሬን የምትነዛ… ተብላ ነበር። በ “ምህረት” ከእስር እንደተፈታች ወደ ኬንያ ተሰደደች። በኋላም ሀገር ሰላም የሆነ ሲመስላት ከስደት ተመለሰች። ይህች ወጣት እትብትዋ ወደተቀበረባት ሃገርዋ ብትመለስም እንደዜጋ የመኖር ዋስትናዋ ግን በአንባገነኖች መዳፍ ስር ሆነ። በኑሮዋ እና በትዳርዋ ዙርያ ካለፈው የባሰ ችግር መጣባት። ባለቤትዋ እስክንድር ነጋ በሽብርተኝነት ተከሶ በፍርደ-ገምድል ዳኛ ለአመታት ተፈረደበት። ቤት ንብረታቸውም በግፍ ተቀማ። ከዚህ በኋላ በመኖር እና ባለመኖር የሚደረግ ምርጫ ውስጥ መግባት ግድ ሆነባት። እናም ባለቤትዋን ወህኒ ቤት ጥላ ዳግም ተሰደደች። እስዋም ሆነች በሰቆቃ የተወለደ ልጅዋ በመንገድ ከመወርወራቸው በፊት ያላቸው አማራጭ ይህ ብቻ ነበር። የሚወዷት ሃገራቸውን ጥለው ከሁለት መቶ በላይ የሚሆኑ ስደተኛ ጋዜጠኞችን ተቀላቀሉ። እንደቀልድ የሚነገር ሌላም እውነታ አለ። ከ”ሽብርተኛ” ጋር በስልክም ሆነ በአካል ያወራ፣ አብሮ የታየ፣ አብሮ ሻይ የጠጣ፣ የተነካካ ሰው ሁሉ ሽብርተኛ እንደሆነ አዋጁ ይደነግጋል። ሰርካለም እና ናፍቆት በእስር ያለው እስክንድር ጋር በሚያደርጉት ግንኙነት ሽብርተኛ ተብለው ሊወነጀሉም ይችሉ ነበር።

በስልጣን ላይ ያሉት ሰዎች ፍርሃት ውስጥ እንዳሉ ግልጽ ነው። በጋዜጠኛ የሚናድ ሀገ-መንግስት ይዘው ስንት አመት ሊዘልቁ እንደሚችሉ ባናውቅም፤ አሁንም ጋዜጠኞችን ሲያስሩ ይህንንኑ ዘፈን ይደጋግሙታል። 99.7 በመቶ በህዝብ የተመረጠ መንግስት መራጩን ሕዝብ ከቶውንም መፍራት አልነበረበትም። ነገሩ ስላቅ ነው። ይህ ቀልዳቸው ግን የህዝቡን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ ከመመልከት የሚመጣ ይሁን እንጂ ጉዳዪ ሌላ ነው። አንባገነኑ ናፖሊዮን ቦናፓርት ብሎታል። ከሺ ሳንጃ አንድ ጋዜጠኛ ያስፈራል። የጭቆና እና የአፈና ስርዓት ገንብቶ ለረጅም አመት የቆየ አንባገነን በታሪክ አልታየም።

የፈቀደውን መምረጥ የሚችልን ህዝብ አዲስ ዘመንን ብቻ እንዲያነብ መምከራቸው ብቻ አይደለም በሕዝብ ላይ ያላቸው ንቀት፤ የፍትህ ስርዓቱን ለበቀል የሚዘረጋ እጃቸው አድርገው ነጻውን ፕሬስ ለማጥፋት ሲጠቀሙበትም እጅግ ያንገበግባል። የህግ የበላይነትን እንዲህ እያደረጉ ናዱት።

ኢሕአዴግ የፕሬስ ነጻነትን ለህዝቡ እንዳጎናጸፈ ይመጻደቃል። ይህ ስህተት ነው። መናገር፣ ሃሳብን በነጻነት መግለጽ፣ መጻፍ፣ … ወዘተ መብት የሰው ልጅ የተፈጥሮ ጸጋ እንጂ አንድ ስርዓት የሚያጎናጽፈን ጉዳይ አይደለም። በሌላ በኩል ደግሞ ይሀው ስርዓት እነዚሁኑ መብቶች እየጨፈለቀ እነሆ ሃያ ሶስት አመታትን ዘልቋል።

ነጻ ፕሬሱን ለምእራባውያን የዲሞክራሲ ማሳያ አድርጎ እንደተጠቀመበት እርግጥ ነው። የአለም ባንክ እና ለጋሽ ሃገሮች በኢትዮጵያ የሳንሱር አዋጅ እንደጠፋ ነው የሚነገራቸው። የእርዳታና ብድር እጃቸውን የሚዘረጉልንም ከቀድሞው የተሻለ የመጻፍና የመናገር ነጻነት አለ ብለው ስለሚያምኑ ይመስላል። ግና ይህ የሳንሱር አዋጅ በአእምሮ ሳንሱር መተካቱን የምናውቀው እኛ ብቻ ነን። ሳንሱር ቢኖር ይህ ሁሉ ጋዜጠኛ ባልታሰረ፣ ባልተንከራተተ እና ባልተሰደደ ነበር።

ምርጫ መጣ! ጋዜጠኛ ይውጣ! እንዲሉ… በቅርቡ በስድስት ነጻ ፕሬስ ህትመቶች ላይ ከተመሰረተው ክስ ጋር በተያያዘ አስራ ሁለት ጋዜጠኞች ለስደት መብቃታቸው ተዘግቧል። በጭላንጭል የነጻነት ድባብ ይንቀሳቀሱ የነበሩት፤ አዲስ ጉዳይ፣ ሎሚ፣ ጃኖ፣ አፍሮ ታይምስ እና እንቁ ጋዜጦች እንዲቋረጡ ተደርጓል። ጋዜጠኞቹም በአሸባሪነት ሽፋን ተከስሰው እስከ አስራ ስድስት አመት የሚደርስ ጽኑ እስራት ተበይኖባቸው የነእስክንድር ነጋ፣ ውብሸት ታዬ እና ርእዮት አለሙ እጣ ይደርሳቸዋል። እነዚህ ጋዜጠኞች የነበራቸው አማራጭ የሽብር አዋጁ ሰለባ መሆን አልያም አገር ለቀው መሰደድ ነው። ተሰደዱ። የስደተኛ ጋዜጠኛውን ቁጥር ወደ 210 አሳደጉት።

ውንጀላው ግን በተያዘለት መርሃ-ግብር ቀጥሏል። ሰሞኑን “ያልተገሩ ብዕሮች” በሚል ርእስ በኢቲቪ የቀረበውን “ዘጋቢ ፊልም” ያስተውሏል? በአንድ በኩል የጋዜጠኖቹ ጉዳይ በህግ የተያዘ እንደሆነ ይነግሩናል። በሌላ በኩል ደግሞ “ልማታዊ” ተዋንያን እና የስርዓቱ አጎብዳጆችን በመገናኛ ብዙሃን አቅርበው ፍርድ እንዲሰጡ ያደርጓቸዋል። በእርግጥ በመገናኛ ብዙሃን እየቀረቡ አንድ ተጠርጣሪን በወንጀለኝነት መፈረጅ አዲስ ነገር አይደለም። የፍትህ አካሉ ውሳኔ ከመስጠቱ በፊት ተጠርጣሪው በኢቲቪ የፖለቲካ ፍርድ ይበየንበታል። ከዚያም እንደ “ዳኛ” ልዑል አይነት የሲቪል ሰርቪስ ምርቶች ውሳኔውን ያጸኑታል።

በዚያ የኢቲቪ ቅንብር ሃይሌ ገብረስላሴም ተዋንያን ነበር። የሚናገረውም የትዬለሌ። “ትልቁ የጦር መሳርያቸው ፕሬስ ነው።… ጦር ከፈታው ወሬ የፈታው ይባላል… ” ይለናል ሃይሌ ገብረስላሴ። “ዘጋቢ” ፊልሙም የእነ እስክንድር ነጋን ፎቶ፣ የእነ ተመስገን ጽሁፎች ያሳየናል። የዚህ ድራማ ሌሎቹ ተዋንያን ከሙያው ጋር የተያያዝን ነን የሚሉ አድርባዮች ናቸው። ሃይሌ ግን ምን ቤት እንደሆነ ግልጽ አይደለም። በየትኛውስ እውቀቱ ነው ፍርድ ሊሰጥ የደፈረው? “አንድ ጋዜጣ የውሃ አምራች ድርጅትን እንዲዘጋ አድርጓል።” ሲል ሃይሌ በዚያ “ዘጋቢ ፊልም” ይወነጅላል። አንድ ጋዜጠኛ እውነትን ጽፎ የንግድ ድርጅትን ወይንም የመንግስት ተቋምን ማፍረስ ወይንም በተቋማቱ ላይ ጥርጣሬ መፍጠር ከቻለ እንዲያውም ጀግና ነው የሚባለው። ጋዜጠናው የሚጽፈው ውሸት ከሆነ ደግሞ ፍርዱን ለህዝቡ ለምን አይተውለትም?

አብራሃ ደስታ ሌላው በአሸባሪነት ሽፋን የተከሰሰ ጋዜጠኛ ነው። አብርሃ አሸባሪ መሆኑ የተረጋገጠው ፍርድ ቤት ሲገባ እና ሲወጣ ነው። ሲገባ በጭብጨባ ሲወጣ በጭብጨባ ተሸኝቷል። ህዝብ በነቂስ ወጥቶ ኣብርሃ ጀግና! የነፃነት ታጋይ! እንወዳሃለን፤እናከብርሃለን ሲለው እነ ሃይሌ ገ/ስላሴ የት ነበሩ?

ያልተገራ አንደበታቸውን በመገናኛ ብዙሃን ሲከፍቱ የነበሩት እነዚህ ተዋንያን የሚነግሩን እጅግ አሳፋሪ ነገር ነው። አጠቃላይ ይዘቱ በመንግስት ላይ ምንም አይነት ትችት መቅረብ የለበትም የሚል እንድምታ አለው። የህወሃትን አንባገነናዊነት መተቸት፣ የስርዓቱ ፖሊሲዎች መንካትና በባለስልጣናቱ ላይ ጥርጣሪ እንዲኖር ማድረግ… ስርዓቱን ያፈርሰዋል ነው እያሉን ያለው። ህግ አውጭው ከህግ አስፈጻሚውን፣ ህግ አስፈጻሚው ደግሞ ህግ ተርጓሚውን እርስ-በርስ የሚቆጣጠሩበት እና የሚያስተከክሉበት አካሄድ በሌለበት ሃገር ነጻው ፕሬስ ከዚህ ውጭ ምን ይስራ ነው የሚሉት? ፕሮፓጋንዳ?

ለፕሮፓጋንዳውማ በርካታ አማራጮሽ አሉ። አዲስ ዘመን ጋዜጣም አለልን። ለ90 ሚሊዮን ህዝብ የቀረው ጋዜጣ። አዲስ ዘመን በቁጥር ስንት ሺ እንደሚታተም ባናናውቅም በኪሎ እየተሸጠ የሸቀጥ እቃ መጠቅለያ ሆነ እንጂ። ‘የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ተመረቁ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ወደ ሱዳን ሄዱ፣ ሃይለማርያም ደሳለኝ ከሱዳን ተመለሱ። የኢትዮጵያ ኢኮኖሚ በ 11 እጅ እንደሚያድግ ሃይለማርያም ደሳለኝ ተናገሩ።’ …. የሚሉ ዘገባዎችን እየያዘ ከሸቀጥ እቃ መጠቅለያነት ውጭ ለሚመጻደቁለት እድገት ምንም እንዳልፈየደ እንኳ አያውቁትም።

የመገናኛ ብዙሃን አፈናው በነጻ ፕሬሱ ላይ ብቻ አልተገደበም። በኢትዮጵያ የመረጃ መረቦችም ታፍነዋል። ከሰብ ሰሃራ አፍሪካ በኢንተርኔት ይዞታ እና አገልግሎት የመጨረሻዋ ሃገር ናት። ኢንተርኔቱን የሚቆጣጠረው መንግስታዊው ቴሌኮም ስርዓቱን የሚተቹ ድረ-ገጾችን በቻይና ቴክኖሎጂ እንዲዘጉ አድርጓል። የዜጎችን ስልክ በህገወጥ ማንገድ መጥለፍ የተለመደ ተግባር ነው። እንዲሁም ስካይፕ እና ቫይበር ያሉ የቮይስ ኦቨር ስልኮች ደግሞ ፊን ፊሸር በተባለ የኮምፒዩተር ቫይረስ አማካኝነት ይጠለፋሉ። እንዲህ እያሉ በዜጎች የግል ህይወት ሳይቀር እየገቡ ቴሌን ሙሉ በሙሉ የስለላ ተቋም እንዳደረጉት የአሜሪካው ሂዩማን ራይትስ ዋች ይፋ አድርጓል።

ኢትዮጵያን ወደ ጨለማ ዘመን እየወሰዳት ያለው ይህ የህወሃት ስርዓት የኢንተርኔት ተጠቃሚው እንዲያሽቆለቁል እየጣረ እንደሆነ ነው መረጃዎች የሚጠቁሙት። በተለይ የፌስቡክ አብዮትን ለመግታት ስለሚሻ የኢንተርኔት አገልግሎትን ማዳከሙ ላይ ጥብቅ አቋም ይዟል። መንግስት አልባዋ ሶማልያ እንኳን፣ ስድስት የቴሌፎንና ስልክ አቅራቢ ኩባንያዎች አሏት። በዚህ ቀላል ቴክኖሎጂ እንኳን ከሶማልያ በታች ሆኖ ስለ እድገት መመጻደቃቸው ሊያፍሩበት ይገባል።

እጅግ የሚያሳዝነው ይህ ስርዓት ለፈጸመው ለዚህ ሁሉ በደል ለሽልማት መብቃቱ ነው። ልማታዊው አርቲስት ሰራዊት ፍቅሬ በአርቲስቶች ስም ለሟቹ ጠቅላይ ሚ/ር የወርቅ ብዕር ነበር ያበረከተላቸው። ብዕር ትልቅ ትርጉም አለው። ብእር የሚሸለም ሰው ለፕሬስ ክብር ያለው፤ ፕሬስን የሚያከብር ሰው ነው። ሰራዊት የወርቅ ብዕር እንዲሸልም አርቲስቶች አልወከሉትም ነበር። ይህንን ሲያደርግ የነጻው ፕሬስ ጋዜጠኞች እስር ቤት ውስጥ ይንገላቱ ነበር። ሰራዊት ይህንን ሲያደርግ የአለም አቀፍ ህብረተሰብ ጠ/ሚኒስትሩን የፕሬስ አፈና በእጅጉ ያወግዝ ነበር። እንደ ሰራዊት ያሉ ሃላፊነት የጎደላቸው ሰዎች ብዙ አይደሉም። ለህሊናቸው ሳይሆን ለሆዳቸው ሲሉ እንዲህ አይነት ስራ እየሰሩ በሰው በቁስል ላይ እንጨት ይሰድዳሉ። ታዲያ እንደነዚህ አይነቶቹ አድርባዮችም ለፕሬሱ መጥፋት ሚናቸው ቀላል አይደለም። የማያልፍ የለም። ሁሉም ያልፋል። መንግስትም እንደ አንሶላ ተጠቅልሎ ይሄዳል። ይህ ቀን አልፎም ለትዝብት ያበቃናል።

ማን ነበር “ፕሬስ የሌለው መንግስት ከሚኖረን መንግስት የሌለው ፕሬስ ቢኖረን እንመርጣለን።” ያለው? እርግጥ ነው። ያለ ፕሬስ የሚኖር ህዝብ በጨለማ ነው የሚጓዘው። ያለ ነጻ አስተሳሰብ እና ያለ ነጻ ፕሬስ፣ እድገት ይመጣል ማለት አይታሰብም። እንዲያው የህዝብን ንቃተ-ህሊና ዝቅ አድርጎ መመልከት ይሆናል እንጂ።

Ginbot 7’s point man in Eritrea arrested

ER

image

Zemene_Kasse

According to new Ethiopian Review report :- Ato Zemene Kasse, the field representative of Ginbot 7 in Eritrea and head of political affairs, has been arrested by Shabia, according to Ethiopian Review sources.

It has been several days since Zemene had disappeared after having an argument with Eritrean intelligence agents about the detention of some young Ethiopians under his command who were recruited by Ato Andargachew Tsige and brought from Uganda and South Africa to Eritrea. Repeated request by him to get an answer for their arrest were ignored by Shabia. Then Zemene himself disappeared and one of his friends who is currently in Sudan confirmed to Ethiopian Review today that he is arrested.

Zemene is arrested simply for asking about the well-being of his comrades.

Shabia’s Eritrea has turned out to be a Bermuda Triangle for Ethiopian heroes such as
Zemene,
Andargachew,
Tadesse,
Fisseha,
Getachew,
Yoseph,
Adane,
Kassahun, and so many others.

መንግስታዊ ሽብርተኝነትን የሚሸከም ትከሻ አይኖረንም!!!

SemayawiParty.org

image

ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም

የህወሓት/ኢህአዲግ አገዛዝ በኢትዮጵያ ስልጣን ላይ ከወጣበት ጊዜ ጀምሮ ዜጎችን በማፈንና በማሰቃየት ብሎም በመግደል የአፈና አገዛዙን ለረጅም ጊዜ ሲያራምድ መቆየቱ ዓለም የሚያውቀው ሀቅ ነው፡፡ በተለይም ባለፉት 10 ዓመታት የህዝብን ሰላማዊ እንቅስቃሴ ለማፈን እስራትና ግድያውን ህጋዊ ለማስመሰል የተለያዩ አፋኝ አዋጆችን አውጥቷል፡፡ እነዚህን አዋጆችንም ተገን አድርጎ በሰላማዊ መንገድ የሚታገሉ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎችንና አባለትን፣ ጋዜጠኞችንና ጦማርያንን፣ እንዲሁም የእምነት ተቋማት መሪዎችን እና በአገዛዙ ላይ ጥያቄ የሚያነሱ ዜጎችን ማሰሩን፣ ማሰቃየቱንና ግድያውን ተያይዞታል፡፡ በህገ መንግስቱ የተካተቱ የሰብዓዊ መብቶችንና ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን በሙሉ የሚጥሰውና የአምባገነንነት ስልጣኑን ለማራዘም ሲል ያፀደቀው የፀረ-ሽብር አዋጅ ከፀደቀበት እለት አንስቶ ኢህአዴግ ለስልጣኔ ያሰጉኛል የሚላቸውን ፍፁም ሰላማዊ ታጋዮችንና ህገ መንግስታዊ መብታቸውን ተጠቅመው በድፍረት የፃፉ ጋዜጠኞችን ብሎም የእምነት ነፃነታችን ይከበር ብለው የጠየቁ የሀይማኖት መሪዎችን በጠራራ ፀሃይ ያለምንም ወንጀል በዚሁ ህገ ወጥ አዋጅ ‹‹የፀረ ሽብር ግብረ ሀይል›› በሚባል ማንነቱ በማይታወቅ የጨለማ ቡድን ወደ እስር ቤት እያጋዘ ይገኛል፡፡

ይህን የሚያጋልጡ ሚዲያዎችንም ለማፈን እስር ቤቶችን ጨምሮ በሚሊዮኖች የሚቆጠር ዶላር እያፈሰሰ የአየር ሞገድ ያውካል፤ በዚህ ሳያበቃ በሀገር ውስጥ በሰላማዊ መንገድ ተቃውሟቸውን የሚያሰሙ ፖለቲከኞችን ለማሸማቀቅ እንደ ኢሳት ያሉ ሚዲያዎችን የአሸባሪ ልሳን ብሎ በመፈረጅ ሚዲያውን የሚጠቀሙትን ደግሞ ከአሸባሪዎች ጋር ንክኪ እንዳላቸው አድርጎ መወንጀሉን ቀጥሎበታል፡፡ እንደሰማያዊ እምነት ማንም አካል መልእክት የሚያስተላለፍበትን የሚዲያ ተቋም ሊመርጥለት እንደማይችል መንግስት እንዲገነዘበው ከዚህ በፊት በግልፅ ያሳወቀ ሲሆን አሁንም ፓርቲው በዚሁ የፀና አቋሙ እንደሚቀጥል በድጋሚ ይገልፃል፡፡

ባጠቃለይ የዚህን ገዢ አካል የእውር ድንብር ሀገር የማስተዳደር ጉዞ ለመታገል በርካቶች በሰላማዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ ቢሆንም በህወሓት/ኢህአዲግ ግፍና መከራ ተገፍተው ስርዓቱን በሃይል እናስወግዳለን ብለው ሀገር ጥለው የተሰደዱ ዜጎችም እንዳሉ ይታወቃል፡፡ የህወሓት/ኢህአዲግ ማናለብኝነትና የስልጣን ጥመኝነትም በግለሰቦች ላይ ከሚያስከትለው ማህበራዊ ቀውስ በላይ በሀገሪቱ ኢኮኖሚያዊና ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ከፍተኛ አለመረጋጋትን አስከትሏል፡፡ በአሁኑ ሰዓትም ይህ ገዢ ፓርቲ የፈጠረው ስርዓት የሀገሪቷን ሰላማዊ የፖለቲካ ምህዳር በማጥበብ ሀገራችንን ወደ አልተፈለገ አለመረጋጋትና ቀውስ እየመራት ይገኛል፡፡ፓርቲያችንም እነዚህን ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም በቅርቡ እየተፈፀሙ የሚገኙ ህገ ወጥ ድርጊቶች ስላሳሰበው ይህን መግለጫ ለማውጣት ተገዷል:-

1. ሰኔ 16 2006 ዓ.ም የየመን መንግስት የዓለም አቀፍ ስምምነቶችንና ድንጋጌዎችን በመጣስና በሰው ሀገር የውስጥ ጉዳይ በመግባት የአማፂ ቡድን ግንቦት ሰባት ዋና ፀሃፊ የሆኑትን አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን መያዟ ይታወሳል፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ህገ-ወጥ በሆነ መንገድ ለህወሓት/ ኢህአዴግ ተላልፈው መሰጠታቸውን ከ16 ቀናት በኋላ መታወቁና ይህንንም ሁለቱ ሀይሎች ማመናቸው ተሰምቷል፡፡ ነፃነት በሌለበት ሀገር ዜጎች ሰብዓዊ ክብራቸውን ለማስጠበቅ የሚያደርጉት ጥረት የሌሎች ሀገር መንግስታት የሚያደርጉትን ጣልቃ ገብነት በዓለም አቀፍ ስምምነቶችም ሆነ በተለይ በሁለቱ ሀገሮች ግንኙነት ላይ ከፍተኛ ጥላ የሚያጠላ መሆኑን ግንዛቤ አለመወሰዱ እጅግ የሚያሳዝን ድርጊት ነው፡፡ አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ከተያዙ በኋላ ላለፉት 16 ቀናት በምን አይነት ሁናቴ እንደቆዩ ህዝብና ቤተሰቦቻቸው እንዲያውቁት አለመደረጉ፤ ስለ አያያዛቸው ሁኔታም በማህበረሰቡና በፓርቲያችን ውስጥ ከፍተኛ ጥርጣሬ እንዲኖር አድርጓል፡፡ሰማያዊ ፓርቲ የአቶ አንዳርጋቸው ፅጌ ሰብዓዊ አያያዝ እያሳሰበው ህወሓት መራሹ የኢህአዴግ አገዛዝ አያያዛቸውን ግልፅ እንዲያደርግ ሰብዓዊ ክብራቸውም እንዲጠበቅ በጥብቅ ያሳስባል፡፡
2. በዚሁ ሳምንት ገዢው ፓርቲ ሐምሌ 1 ቀን 2006 ዓ.ም ፍፁም ሰላማዊ በሆነ መንገድ የአምባገነኑን መንግስት ህወሓት/ኢህአዲግን ሲታገሉ የነበሩ ፖለቲከኞችን በስመ አሸባሪ ከያሉበት እየለቀመ ህገ-ወጥ እስራት መፈፀሙ ይታወቃል፡፡ ህወሓት/ኢህአዲግ ይህ ግብታዊ ተግባሩ ምንም እንኳን አዲስ ባይሆንም በአሁኑ ወቅት ለውጥን ለማምጣት በቆራጥነት እየታገሉ ያሉ ሰላማዊ ታጋዮችን ማሰሩ በሀገር ውስጥ በህጋዊ መንገድ እየተንቀሳቀሱ የሚገኙ ፓርቲዎችን ከአማፂ ቡድኖች ጋር ግንኙነት ያላቸው በማስመሰል ሰላማዊ ትግሉን ለማዳከምና መጪውን 2007 ዓ/ም ምርጫ ያለ ተቀናቃኝ ለማለፍ የሚደረግ ህገ ወጥ እንቅስቃሴ መሆኑን ተገንዝበናል፡፡ የፓርቲያችን ብ/ም/ቤት ምክትል ሰብሳቢ የሆነው አቶ የሺዋስ አሰፋ በሰላማዊ ትግሉ በቁርጠኝነት እየተሳተፈ ባለበት ሁኔታ ለእስር መዳረጉ፤ የአንድነት ፓርቲ ህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ሀብታሙ አያሌው፤ የአንድነት ፓርቲ የድርጅት ጉዳይ ምክትል ሀላፊ አቶ ዳንኤል ሺበሺ እና በሰሜኑ የሀገራችን ክፍል ከፍተኛ የህዝብ ንቅናቄን በመፍጠር ላይ ያለው የአረና /ትግራይ/ ፓርቲ አመራር አባል የሆኑትን አቶ አብረሃ ደስታ ለእስር መዳረጋቸው ህወኃት/ኢህአዴግ የመጨረሻው መጨረሻ ምዕራፍ ላይ መድረሱን ያረጋግጣል፡፡ በመሆኑም አገዛዙ እያካሄደ ያለውን መንግስታዊ ሽብር አቁሞ ለሀገርም ሆነ ለራሱ የሚበጀውን መንገድ እንዲከተል እያሳሰብን የታሰሩት የፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች በአስቸኳይ እንዲፈቱ እንጠይቃለን፡፡

በመጨረሻም ፓርቲያችንን መንግስት እያደረገ ያለው ሽብርን የመንዛትና ህግን የመጣስ ተግባሩ መቼም ቢሆን ከሰላማዊ ትግሉ እንደማያቆመውና ሰላማዊ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል በአፅንኦት እየገለፀ እነዚህንና ከላይ የተጠቀሱትን የገዢውን ፓርቲ መርህ አልባነት፣ ህገ-ወጥነት እና የለየለት አምባገነንነትን አሁን ካለው ነባራዊ እውነታ ጋር አጣምሮ የትግል ስልቱን ደረጃ ከፍ ወዳለ ምዕራፍ ማሸጋገር እንዳለበት አምኗል፡፡ በመሆኑም ከዚህ በኋላ ለምናደርጋቸው ሀገር አቀፍ ንቅናቄዎች መላው የሀገሪቱ ህብረተሰብ በንቃት ተዘጋጅቶ እንዲጠብቅ ጥሪውን እያስተላለፈ ለዚህም ቁርጠኛ አመራር ለመስጠት ዝግጁነቱን ለመግለፅ ይወዳል፡፡በዚህ አምባገነንነትን ለመታገል በሚደረገው ንቅናቄም በሀገር ውስጥ የሚገኙ ህጋዊና ሰላማዊ ፓርቲዎች፤አለም አቀፍ ተቋማት፤የሰብአዊ መብት ተሟጋቾች፤ሲቪክ ማህበራት፤መላው ኢትዮጵያውያንና ትውልደ ኢትዮጵያውያን ከሰላማዊ ትግሉ ጎን በጋራ እንድንቆም እንጠይቃለን፡፡

ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር
ሰማያዊ ፓርቲ
ሀምሌ 3/2006ዓ/ም

Extradited Ethiopian activist on ETV

BBC

image

Andargachew Tsege, a UK national, leads the banned Ginbot 7 movement
Opposition leader Andargachew Tsege has appeared on Ethiopian state television, following his disappearance from Yemen last month.

His UK-based wife Yemi Hailemariam told the BBC she was shocked to see him on television.

Yemen arrested Andargachew while he was in transit at Sanaa airport, and secretly handed him to Ethiopia.

In 2009, Andergachew was sentenced to death in absentia for planning to assassinate government officials.

Andergachew, a UK national, denied the charge.

He is secretary-general of Ethiopia’s banned Ginbot 7 movement.

Ms Yemi said it was difficult to see footage of her husband.

“I switched it off quickly. I couldn’t watch it,” she said.

Ms Yemi said the UK should demand the immediate release of her husband.

“If they want to try him, they must go through the proper channels,” she told the BBC.

Ginbot 7 says Andargachew had been on his way from the United Arab Emirates to Eritrea when he was detained at Sanaa airport.

Ginbot 7 (15 May) was named after the date of the 2005 elections, which were marred by protests over alleged fraud that led to the deaths of about 200 people.

BBC

Yemen Unlawfully Deported Andargachew Tsige, Concerns over Possible Mistreatment

Human Rights Watch

image

(London) – An exiled Ethiopian opposition leader unlawfully deported by Yemen back to Ethiopia is at risk of mistreatment including torture. Andargachew Tsige is secretary-general of Ginbot 7, a banned Ethiopian opposition organization, and was convicted and sentenced to death in absentia in separate trials in Ethiopia in 2009 and 2012.

The current whereabouts of Andargachew, a British national, is unknown, raising concerns for his safety. The Ethiopian government should take all necessary steps to ensure Andargachew’s safety and his right to a fair trial. Many individuals arrested in politically related cases in Ethiopia are detained in Addis Ababa’s Maekelawi prison. In an October 2013 report, Human Rights Watch documented the use of torture by authorities against detainees in Maekelawi, including members of opposition political parties and organizations, as well as journalists.

“We are deeply concerned for Andargachew Tsige’s safety,” said Leslie Lefkow, deputy Africa director. “Ethiopia needs to demonstrate that it is holding Andargachew in accordance with its international obligations, and he should be allowed immediate access to a lawyer, his family, and to British consular officials.”

Yemeni officials arrested Andargachew at El Rahaba Airport in Sanaa, Yemen, on June 23 or 24, 2014, while he was in transit on a flight from Dubai to Eritrea. They did not permit him consular access to UK embassy officials and summarily deported him to Ethiopia, credible sources told Human Rights Watch, despite his being at risk of mistreatment.

Yemeni authorities initially denied any knowledge of Andargachew’s detention and transfer to Ethiopia. Ethiopian government officials publicly called for his extradition from Yemen on July 3.

Under the Convention against Torture, which Yemen ratified in 1991, a government may not “expel, return (‘refouler’) or extradite a person to another State where there are substantial grounds for believing that he would be in danger of being subjected to torture.” These protections override any extradition treaty or other security arrangement that may exist between Yemen and Ethiopia.

Trials in absentia generally violate the defendant’s right to present an adequate defense, concerns heightened in cases involving the death penalty.

“Yemen blatantly violated its international legal obligations by deporting someone to Ethiopia who not only is at serious risk of torture, but also faces the death sentence after being tried in absentia,” Lefkow said.

Ginbot 7, of which Andargachew is a founding member, was established in the aftermath of Ethiopia’s controversial May 2005 national elections. The Ethiopian government banned Ginbot 7, which has advocated the armed overthrow of the Ethiopian government, and officially considers it to be a terrorist organization.

The government has prosecuted Ginbot 7 members and leaders in trials that did not meet international fair trial standards. In November 2009, a court convicted Andargachew and 39 others under the criminal code on terrorism-related charges. Andargachew, who was tried in absentia, was sentenced to death. In June 2012, he was convicted again in absentia, this time under the abusive 2009 anti-terrorism law,along with 23 journalists, activists, and opposition members. Again, he was sentenced to death.

Human Rights Watch has repeatedly criticized provisions in Ethiopia’s anti-terrorism law that violate due process rights guaranteed under Ethiopian and international law. At least 34 people, including 11 journalists and four Ginbot 7 leaders, are known to have been sentenced under the law since late 2011 in what appeared to be politically motivated trials; the real number is likely much higher. Suspects held under the law may be detained for up to four months without charge, among the longest periods under anti-terrorism legislation worldwide.

Ethiopian courts have shown little independence from the government inpolitically sensitive cases. Defendants have regularly been denied access to legal counsel during pretrial detention, and complaints from defendants of mistreatment and torture have not been appropriately investigated or addressed – even when defendants have complained incourt.

The Ethiopian government routinely denies that torture and mistreatment occurs in detention. It restricts access to prisons for international observers, monitors, and consular officials, making it difficult to monitor the number and treatment of prisoners. In several cases documented by Human Rights Watch, Ethiopian security officials have arrested foreign nationals, denied knowledge of their whereabouts, and delayed access for consular officials for long periods.

In 2007 Human Rights Watch documented the forced transfer of scores of men, women, and children from Somalia and Kenya to Ethiopia. One of the men, Bashir Makhtal, a Canadian citizen of Ethiopian origin who was accused of membership of the Ogaden National Liberation Front (ONLF), a banned armed movement in Ethiopia, was denied consular access for 18 months. Meanwhile in 2010 and again in 2012, refugees registered with the United Nations High Commissioner for Refugees in Kenya were unlawfully returned to Ethiopia and told Human Rights Watch that they were subsequently tortured in detention. In all of these cases, the individuals were accused of belonging to groups that the Ethiopian government has designated as terrorist groups.

“Given its appalling track record of mistreating members and perceived supporters of banned groups, Ethiopia should know that the world will be watching how it treats Andargachew Tsige,” Lefkow said.

 

Ethiopian activist at risk of torture 

Amnesty International 

image

Andargachew TsegeAndargachew Tsige, an Ethiopian political activist in exile, appears to have been arrested in transit in Yemen on 24 June and forcibly returned to Ethiopia. He is at risk of torture and other ill-treatment. Andargachew Tsige is a British national of Ethiopian origin and Secretary-General of Ginbot 7, an outlawed Ethiopian opposition group. He disappeared on 24 June at Sana’a airport in Yemen, while in transit between the United Arab Emirates and Eritrea. Although no official statements have been released by the Yemeni or Ethiopian authorities about his current whereabouts, human rights activists in Yemen told Amnesty International that he was forcibly returned to Ethiopia the same day he landed after being detained at the Sana’a airport.

He is at high risk of torture and other ill-treatment in Ethiopia, where political detainees are frequently tortured in order to extract information and confessions. His incommunicado detention in an unknown location increases this risk.

Ginbot 7 is one of five organisations proscribed as terrorist organisations by the Ethiopian parliament in 2011. In 2012, Andargachew Tsige was prosecuted in absentia on terrorism charges (alongside journalist and prisoner of conscience Eskinder Nega, and others) and sentenced to life imprisonment. Previously, in 2009, he was convicted in absentia on charges related to an aborted coup attempt and was sentenced to death. He was also tried in absentia in the 2005-2007 trial of political opposition members, journalists, activists and others.

In recent years, many Ethiopians wanted by the authorities on the grounds of their political activities have been kidnapped in neighbouring countries and forcibly returned to Ethiopia. This has often involved the collaboration of security forces in those countries. Another of the defendants in the 2012 trial had been kidnapped and forcibly returned from Sudan. All those returned are at risk of arbitrary detention, torture and unfair trial.

Please write immediately in Amharic, English or your own language: ? Calling on the authorities to guarantee Andargachew Tsige is not subjected to torture or other forms of ill- treatment; ? Calling on the authorities to immediately provide information on the location where he is being held, and to ensure that he has full and immediate access to legal and consular representation and family members; ? Calling on the authorities to ensure that Andargachew Tsige is not required to serve any sentence for a conviction in absentia and must be retried on any charges against him in a trial that meets international standards, before a new court and without the possibility of the death penalty.

PLEASE SEND APPEALS BEFORE 8 AUGUST 2014 TO: Minister of Justice Berhanu Hailu Ministry of Justice, PO Box 1370, Addis Ababa, Ethiopia Fax: +251 11 5517755 Salutation: Dear Minister

Minister of Federal Affairs D. Shiferaw Teklemariam Ministry of Federal Affairs P.O.Box 5718 Addis Ababa, Ethiopia Email: shiferawtmm@yahoo.com Salutation: Dear Minister

And copies to: Prime Minister His Excellency Hailemariam Desalegn Office of the Prime Minister, PO Box 1031, Addis Ababa, Ethiopia Fax: +251 11 552030 (keep trying)

Also send copies to diplomatic representatives accredited to your country. Please insert local diplomatic addresses below: Name Address 1 Address 2 Address 3 Fax Fax number Email Email address Salutation Salutation Please check with your section office if sending appeals after the above date.

URGENT ACTION ETHIOPIAN ACTIVIST AT RISK OF TORTURE

ADDITIONAL INFORMATION Andargachew Tsige is a former member of the ruling Ethiopian People’s Revolutionary Democratic Front (EPRDF) party and was Deputy Mayor of Addis Ababa from 1991 to 1994, when he resigned on account of differences with the government.

Based in the UK, he travelled to Ethiopia shortly before the 2005 elections to support the opposition party Coalition for Unity and Democracy (CUD). On 8 June 2005, in the wake of the controversial election results, he was detained in Ethiopia and held at Ziway army camp. He was released on bail in July of that year. Like many detainees, Andargachew was accused of organizing the demonstrations, seeking to subvert the Constitution and other offences, which he denied, but he was not formally charged with any offence. After he was released he returned to the UK, but was subsequently named, tried and convicted in absentia in a major political trial of the leadership of the CUD, journalists, human rights activists and others, on charges including high treason, in 2005-2007. At the time he was the CUD representative in the UK.

After the CUD trial, fellow defendant Berhanu Nega founded the ‘Ginbot 7 Movement for Justice, Freedom and Democracy’ from exile in the US, of which Andargachew Tsige became Secretary General. Berhanu Nega was also tried in absentia in the 2009 and 2012 trials.