“ኢትዮጵያ ምን ትመስላለች?” ብላ ትጠይቀኝ ነበር እናቴ

Hiwot Emishaw

  1. ጩኸቱ ሁሉ ‹‹በአውሎ ንፋስ ውስጥ የነበረ ፉጨት›› ሆነ ቀረ እንጂ፤ በዚያ ሰሞን ‹‹ኡ ኡ!›› ሲባልበት የነበረውን በድንበር ማካለል ሽፋን ለሱዳን መሬት አሳልፎ የመስጠት ጉዳይን መቼም ታስታውሱታላችሁ፡፡

    ወዳጄ አንተነህ ይግዛው ፤ ይህንኑ ጉዳይ በራሱ መንገድ አይቶት እንዲህ አድርጎ ፅፎታል፡፡
    ስለወደድኩት ለእናንተ አመጣሁት፡፡

    ‹‹የሶስተኛ ክፍል ተማሪ እያለሁ፤
    “ኢትዮጵያ ምን ትመስላለች?” ብላ ትጠይቀኝ ነበር እናቴ፡፡
    “ጀበና!” ስል እመልስላት ነበር እኔ፡፡
    እንደማስታውሰው ይህ ጥያቄ፣ ያኔ የጂኦግራፊ ጥያቄ ነበር ፡፡ መልሱም የጂኦግራፊ፡፡
    .
    ዩኒቨርስቲ የሶስተኛ አመት ተማሪ እያለሁ፤
    “ኢትዮጵያ ምን ትመስላለች?” ብላ ብትጠይቀኝ እናቴ…
    “አንገት የሌላት ጀበና” እላት ነበር እኔ፡፡
    አሁንም ጥያቄው የጂኦግራፊ ሊሆን ይችላል፡፡ መልሱ ግን የፖለቲካ፡፡
    .
    ነገስ?…
    ነገም፤ “ኢትዮጵያ ምን ትመስላለች?” ትለኝ ይሆናል እናቴ ፡፡
    እኔስ ምን ብዬ እመልስላት ይሆን?
    “እጀታ የሌላት ጀበና”?…
    ነገም ጥያቄው የጂኦግራፊ ሊሆን ይችላል፡፡

    መልሱስ?