Ethiopia:Land of Extremes -Documentary by BBC

03 April 2014

BBC

http://www.magnificentethiopiatours.com

Magnificent Ethiopia Tours is considered among the most successful and reputed tour Operation Company in Ethiopia in terms of professionalism and quality services, family run and has many years of experience in the tourism industry. We know how much more enjoyable traveling can be when someone you trust looks out for your interests.

http://youtu.be/Li9iNL1s5pk

የኢትዮ ሱዳን ድንበር ከአፄ ፋሲል እስከ ኢህአዴግ

29 March 14

የአፄ ፋሲል ታሪከ ነገስታቸው በኢትዮጵያ ምዕራብ ዛሬ የሱዳን ግዛት በሆነው አገር ስናርን እና ኑብያን እንዳስተዳደሩ ይገልፃል። በኑብያም በርሳቸው ስር የሚተዳደር ጊዮርጊስ የሚባል የአካባቢ ንጉስ አንግሰው እስከ የግብፅ ወሰን የሆነው ጠረፍ ቦታ ድረስ እንዳስተዳደሩ እና የፈረሶቻቸውም መታሰሪያ እና መቀለቢያ ስናር ነበር በማለት ያትታል። አያይዞም ከአፄ ፋሲል በፊት የነበሩት ነገስታት ኑብያንና ስናርን እየዘመቱ ካስገበሩ በኋላ መመለስ እንጂ እንደርሳቸው በስርዐት አላስተዳደሩትም ነበር ብሎ በመግለፅ በእሳቸው ጊዜ አዝማሪ እንደሚከተለው እንደዘፈነ ይጠቅሳል፦ጎንደር ቢያጉረመርም ፋሲል ፈረስህ
ኑብያና ስናር ወርቁን ጫኑልህ
ሣሩን ተጠየፈ የፋሲል ፈረሱ
ክምር የሱዳን ወርቅ ገፈራው ነው ለእሱአፄ እያሱ (አድያም ሰገድ) ወይም ታላቁ እያሱ በአያታቸው በአፄ ፋሲል እየተዳደረ ሲገብር የነበረውን እና በመሀል ያቆመውን ከከሰላ እስከ ስናር ያለውን ወረዳ ጭፍሮቻቸውን በመላክ እንዲያቀኑት በማስደረግ እና የአካባቢው መሳፍንቶች አቋርጠውት የነበረውን ግብር እንዲከፍሉ አሳምነዋል። የአፄ እያሱ (አድያም ሰገድ) የሰሜን ምዕራብ ግዛታቸው ወሰንም ከምዕራብ እስከ ስናር ከሰሜን የከረንን የሐባብን ሀገር ሁሉ ይዞ እስከ ላይኛው የባርካ ወንዝ ድረስ ያካተተ እንደነበር ታሪከ ነገስታቸው ያትታል።የአፄ በካፋ እና የቋረኛዋ እቴጌ ምንትዋብ ልጅ የሆኑት ቋረኛ እያሱ (ብርሀን ሰገድ) ዛሬ የሱዳን ግዛት በሆነው አገር ድረስ ግዛታቸውን በማስፋፋት እና አስተዳደራቸውን በመዘርጋት ግብር እንዳስገበሩ አሁንም የእሳቸው ታሪከ ነገስት ያስረዳል። ግዛታቸውም በአፄ ኃይለሥላሴ ጊዜ እንደወሰን የሚታየውን አትባራን አልፎ ስናር የሚባለውን ከተማ ሁሉ ያካትት ነበር። በጊዜው የስናር ባላባት የነበረው ባዲ ኢብን ሻሉክ የሚባል ሰው ሲሆን እርሱም አልፎ አልፎ ለንጉሱ አልገብርም እያለ የሚያምፅ ቢሆንም ቋረኛው ንጉስ አፄ እያሱ በተደጋጋሚ ወታደሮችን እየላከ የሚቀጣውን እየቀጣ በማሳመን እና በማስገበር አካባቢውን አስተዳድሯል። ከዚያ በኋላ ዘመነ መሳፍንት ገባ እና ነገሮች እንዳልነበሩ ሆኑ።

በዘመነ መሳፍንት ማብቂያ ገዳማ ደግሞ ዳግማዊ አፄ ቴዎድሮስ በሽፍትነት ዘመናቸው ጭፍሮቻቸውን ይዘው ሲንቀሳቀሱበት የነበረው አካባቢ አሁን በሱዳን ይዞታ ውስጥ የሚገኘው ጋላባት እና ዙሪያውን ነበር። ቴዎድሮስም የዘመነ መሳፍንት የአካባቢ ገዢዎችን ተራ በተራ በመውጋት ሁሉንም አሸንፈው ንጉሰ ነገስት ዘ ኢትዮጵያ እንዲባሉ ከፍተኛውን ድርሻ ያበረከተው ከዚሁ ከጋላባት እና ቋራ አካባቢ የተውጣጣው ሠራዊታቸው ነበር። ንጉሰ ነገሥት ከተሰኙ በኋላም አካባቢው በእሳቸው ቁጥጥር የነበረ ሲሆን እንዲያስተዳድር ያደረጉትም የአካባቢው ተወላጅ የሆነውን እና የሽፍትነት ጓደኛቸው እንዲሁም የልብ ወዳጃቸውን እንድሪሥን ነበር።

ከአፄ ዮሀንስ ዘመነ መንግስት ማብቂያ ገዳማ ጀምሮ ኢትዮጵያን በወሠን የሚያካልሏት እንዳሁኑ ያገር ተወላጆች የሚመሯቸው መንግስታት እነ ጅቡቲ፣ ሶማሊያ፣ ኬንያ፣ ዩጋንዳ፣ ሱዳን ሳይሆኑ እነሱን ለመቀራመት እና ቅኝ ለማድረግ በበርሊኑ ኮንፈረንስ በስምምነት የተከፋፈሏቸው አውሮፓውያን አገሮች ናቸው። እነሱም እንግሊዝ፣ ጣልያን እና ፈረንሳይ ነበሩ። አፄ ምኒልክም ከአድዋ ድል በኋላ የወሰን ክልል የተዋዋሉት ከነዚሁ መንግስታት ጋር ነበር።

የእንግሊዝ መንግስት በሱዳን በኩል ስላለው የግዛቱ ወሰን ሌተና ኮለኔል ዢሀን ሐሪንግተን በእንግሊዝ ንጉሥ በኤድዋርድ ሰባተኛ ሥም፤ በኢትዮጵያ በኩል ደግሞ አፄ ምኒልክ በራሳቸው ሥም እ. ኤ. አ. ግንቦት 15ቀን 1902 በአምስት አንቀፅ የተከፈለ ውል ተዋውለዋል። ይህ የአፄ ምኒልክ ውል አሁን መንግስት እንደሚያወራው መተማን፣ ቋራን፣ ከፊል ሁመራን፣ የቤንሻንጉል ጠረፍ አካባቢዎችን የሱዳን ያደረገ አይደለም። የድንበር አወሳሰኑ በካርታ ላይ እንጂ በመሬት ላይ የተከናወነ አልነበረም። ከዚያ በኋላ ኢትዮጵያን ለረጅም ጊዜ በመሩት በኃይለ ሥላሴ ዘመንም የተካሄደ አንድም የድንበር ስምምነት የለም።

ምንም እንኳ ሀፍረት የለሹ የዘመኑ ጠቅላይ ሚኒስተር እኛ ለሱዳን የሰጠነው አንድም አዲስ መሬት የለም ነገር ግን የድንበር ማካለል ያደረግነው በምኒልክ፣ ኃይለሥላሴ እና በሶሻሊስቱ ደርግ ዘመን በሁለቱ መንግስታት የተደረጉ ውሎችን መሰረት በማድረግ ነው፤ ቢሉም በቅርቡ ሌ/ኮ መንግስቱ ሀይለ ማርያም በራሳቸው አንደበት ከሱዳን ጋር እሳቸውም ሆኑ ከእሳቸው በፊት የነበረው የኃይለ ሥላሴ መንግሥት ምንም አይነት የድንበር ውል እንዳላደረገ በመመስክር ድርጊቱን ኢህአዴግ ወደ ሥልጣን ከመጣበት ዘመን ጀምሮ እያካሄደ ያለውን ጥንታዊት ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሌላኛው ተግባር እንደሆነ ገልፀዋል።

የኢትዮጵያን የሰሜን ምዕራብ የሱዳን አዋሳኝ መሬቶችን ያስደፈረው ኢህአዴግ ነው እንላለን! ኢህአዴግ በትጥቅ ትግሉ ዘመን ሱዳን ላደረገችለት እርዳታ እንደውለታ በመቁጠር እንዲሁም ወደፊት ደግሞ የትጥቅ ትግል በማድረግ ኢህአዴግን እንቀብረዋለን ለሚሉ ኢትዮጵያውያን ድጋፍ እንዳትሠጥ እና መመሸጊያ እና መንቀሳቀሻ ቦታወችን እንዳትፈቅድ እንደ ማባበያ ለሙን የሰሜን ምዕራብ መሬት ለግሷታል። ተራ የሥልጣን ፍላጎትን ለማርካት የአገር ሉዐላዊ ደንበርን ለድርድር በማቅረብ እና ለባዕዳን አሳልፎ በመሥጠት በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያው አገዛዝ ኢህአዴግ ነው። ይህንን ደግሞ በአካልም በቁምም የሞቱት ሁለቱ ጠቅላዮቻችን በራሳቸው አንደበት ፓርላማ ላይ ደስኩረዋል በተግባርም አረጋግጠዋል (በተለይ መለስ ይሄን ሲናገር የሱዳን መሪ እንጂ የኢትዮጵያ መሪ አይመስልም ነበር)። የአካባቢው ነዋሪዎችም ወደ ጎንደር እና ሁመራ በመፈናቀል ላይ ናቸው። ለዚህ ሁሉ ተጠያቂው አልበሽር ወይም የሱዳን መንግስት ሳይሆን መለስ ዜናዊ እና የሙት ራዕይ የሚያስፈፅሙት ጠፍጥፎ የሰራቸው የሱ ተከታዮች ብቻ ናቸው አለቀ!!

Pharrell Williams – Happy (Addis Ababa, Ethiopia)

Neva Stopinšek Neva Stopinšek·

Hello everyone!
We are Dunja Maslic and Neva Stopinsek, both students at University of Zagreb, Faculty of Organization and Informatics Varazdin. We’re currently doing our internship in Addis Abbaba, Ethiopia, one within SisCatalyst project and the other with AIESEC student organization. The purpose of this video was to promote organizations we’re working with and to encourage all of you to make a step and create your own unforgettable African story.
Because „Whenever you give a little love, it comes right back”. And it is THAT simple.

Bok svima!
Mi smo Dunja Maslić i Neva Stopinšek, obje studentice Sveučilišta u Zagrebu, Fakulteta organizacije i informatike Varaždin. Trenutno odrađujemo studentsku praksu u glavnom gradu Etiopije, Adis Abebi, od kojih je jedna unutar SisCatalyst projekta, a druga preko studentske organizacije AIESEC. Svrha ovog videa je promovirati organizacije s kojima radimo i ohrabriti sve vas da učinite potreban korak te sami kreirate svoju nezaboravnu afričku priču.
Jer „Svaka ljubav koju dajemo uvijek nam se vraća”. I doista je tako jednostavno!

ኢህአዴግን የምደግፍበት አንድ ነገር አገኘሁ- መሬት አይሸጥም አይለወጥም!

    • 28 March 2014

      Fasil Yenealem

      ለመጀመሪያ ጊዜ ኢህአደግን የምደግፍበት ነገር አግኝቻለሁ። ኢህአዴግ በመቃብሬ ላይ ካልሆነ መሬት አይሸጥም አይለወጥም ይላል። ትክክለኛና ብራቮ የሚያስብል አቋም ነው።
      መሬት የሃብት ሁሉ ምንጭ ነው፤ መሬት ያለው “ምንም” ነገር ባይኖረው ሃብታም ነው። ከጊዜ በሁዋላ እንኳንስ የእርሻና የቤት መስሪያ ቦታ ማግኘት ቀርቶ ለመቀበሪያ የሚሆን ቦታ ማግኘትም ጭንቅ ይሆናል – የሰው ልጅ እንደ አሜባ በፍጥነት ይራባል፣ መሬት ደግሞ በዛው ልክ እየጠበበች ትሄዳለች። እናም ይህን ብርቀየ ሃብት በስርዓት መንከባከብ ግድ ይላል።
      መሬት በግለሰቦች እጅ መሆኑ ምርትን ለማሳደግ ይጠቅማል የሚለው መከራከሪያ አሳማኝ ነው ። ኢህአዴግ ገበሬውንና የከተማውን ሰው እንደፈለገ የሚቆጣጠረው መሬት የመንግስት ስለሆነ ነው የሚለው መከራከሪያም እንዲሁ አሳማኝ ነው። ለመሬቱ ሲል ፈቅዶ የኢህአዴግ ባሪያ ለመሆን የመረጠ ብዙ ወገን አለ፤ መሬትን ነጻ ማድረግ ኢህአዴግ ከዘረጋው የባርነት ቀንበር ነጻ ለመውጣት አንድ እርምጃ ነው ተብሎም ሊታሰብ ይችላል። እርግጠኛ ባልሆንም እያመነታሁ እቀበለዋለሁ። ። በአጭሩ መሬት ወደ ግለሰቦች መዞሩን በመርህ ደረጃ እደግፋለሁ። ነገር ግን ዘረኝነትና ሙሰኝነት ባህሪው በሆነው መንግስት ስር ሆነን፣ መሬት ወደ ግል ይዙር ቢባል ከጥቅሙ ይልቅ ጉዳቱ የሚያመዝን ይመስለኛል ፣ ከኢህዴግ ባርነት ነጻ እንወጣለን ስንል የዘመናት ባርነትን እንዳንከናነብ እሰጋለሁ ። ኢህአዴግ ፍትሃዊ በሆነ መልኩ መሬትን ወደ ግል የማዞር ብቃት የለውም። ይህን ደግሞ በ1980ዎቹ፣ በአማራ ክልል የመሬት ክፍፍል በተደረገበት ወቅት አይተነዋል። ሰዎች በፖለቲካ አቋማቸው ብቻ መሬት እንዳያገኙ መደረጉን በጊዜው ይወጡ የነበሩትን ዘገባዎች አይቶ ማረጋገጥ ይቻላል።
      አዲስ ስርአት እስኪመጣ መሬት ወደ ግል ባይዞር በብዙ መልኩ ተመራጭ ነው።
      ባለፉት 23 ዓመታት ዋና ዋና የሚባሉ የከተማ መሬቶችን የህወሃት ሹሞችና ተላላኪዎቻቸው ተቆጣጥረዋቸዋል። ከከተሞች አልፎ በገጠር ለም የሚባሉትን የእርሻ መሬቶችንም እየተቆጣጠሩዋቸው ነው። ጋምቤላ፣ ኦሮምያ፣ ቤንሻንጉል፣ አፋር እንዲሁም ሰሜን አማራ ብትሄዱ ሰፋፊ መሬቶች በዘመኑ ሰዎች የተያዙ ናቸው። በአዲስ አበባ በአንድ ወቅት በተደረገ ጥናት አብዛኞቹ የከተማዋ ቁልፍ መሬቶች በህወሃትና ተላላኪዎቻቸው የተያዙ መሆኑ ተረጋግጧል ። መሬትን እየተሽቀዳደሙ የመያዙ እሩጫም በቀላሉ የሚቆም አይመስልም፣ አይቆምም። በሚቀጥሉት 5 ዓመታት ( ኢህአዴግ በህይወት ከኖረ) እስካሁን ያልተያዙት ሰፋፊ የእርሻና የከተማ ቦታዎች በጥቂት የዘመኑ ባለሃብቶች ቁጥጥር ስር እንደሚውሉ ለመተንበይ ሼህ ጅብሪል ወይም የፍጥሞውን ዮሃንስ መሆንን አይጠይቅም። ምክንያቱም ግልጽ ነውና ። መሬት የሃብት ምንጭ ነው፤ ሃብት ያለው ጉልበት አለው፤ ጉልበት ያለው ስልጣን አለው፤ ስልጣን ያለው ሁሉም አለው ።
      አሁን ባለው መንግስት መሬት ወደ ግል ይዞታ ይዙር ማለት ላለፉት 22 ዓመታት ሰፋፊ መሬቶችን ዘርፈው የያዙ የዘመኑ ባለሃብቶች የግል መሬት እንዲኖራቸው መፍቀድ ማለት ነው። የሚመጣው መንግስት የእነዚህን ባለሃብቶች መሬት ቀምቶ ለማከፋፈል ቢሞክር ከአለማቀፍ ድርጅቶች ሳይቀር ከፍተኛ ተቃውሞ ይገጥመዋል። በደርግ ዘመን የግል ባለሀብቶች ንብረት ወደ መንግስት በዞረበት ወቅት ከምእራባዊያን አገራት ትልቅ ተቃውሞ መነሳቱን አንዘነጋም። አሁን ባለው የአለም ስርአት የግል ባለሀብቶችን መንካት ማለት ከምእራባዊያንና ከገንዘብ ተቋሞቻቸው ጋር መላተም ማለት ነው። ይሄ መንግስት እስከሚለወጥ መሬት በመንግስት እጅ ከቆየ፣ መጪው መንግስት የእነዚህን ሰዎች መሬት ቀምቶ ለማከፋፈል ቢሞክር ከየትኛውም ወገን ተቃውሞ አይደርስበትም፣ ምክንያቱም መሬት የመንግስት ነውና። ” አስፈላጊው ካሳ ተሰጥቷቸው መሬታቸው ቢቀማ ተቃውሞ አይኖርም ” ቢባል እንኳ፣ በህገወጥ መንገድ ለያዙት መሬት ካሳ መክፈል የሞራልና የፍትሃዊነት ጥያቄ ያስነሳል። አዲሱ መንግስት የኢትዮጵያን የመሬት ስሪት በደንብ አጥንቶና ሁኔታዎችን ሁሉ አመቻችቶ መሬት ወደ ግል ቢያዞር ያን ጊዜ ቁጥር አንድ ደጋፊ እሆናለሁ። ዝምባብዌ ነጻ ከመውጣቱ በፊት መሬት የመንግስት ቢሆን ኖሮ፣ ነጻ በወጣ ማግስት መሬት ከግለሰቦች እየቀማ ያከፋፈለው የዝምባቡዌ መንግስት አሁን የገጠመውን ተቃውሞ ያክል አይገጥመውም ነበር፤ ደቡብ አፍሪካም ነጻ ሲወጣ መሬት የመንግስት ቢሆን ኖሮ፣ የደቡብ አፍሪካ መንግስት ለብዙ ጥቁሮች መሬት እንደፈለገ ለማከፋፈል አይቸግረውም ነበር። በኢህአዴግ ዘመን መሬት ቢከፋፈል የዝምባብዌና የደቡብ አፍሪካ እጣ ይገጥመናል። መሬቱ ሁሉ በጥቂት የዘመኑ ሰዎች እጅ ይገባና እነሱ ” ነጮች” እኛ “ጥቁሮች” እንሆናለን። መጪው መንግስት መሬትን በፍትሃዊነት ማከፋፈል ይችል ዘንድ መሬት በመንግስት እጅ ሆኖ መቆየት አለበት። ኢህአዴግ መውደቁን ካወቀ፣ መሬትን ወደ ግል አዙሮ ለመጪው መንግስት ችግር አውርሶት ያልፍ ይሆን እያልኩ እሰጋለሁ።
      በኢህአዴግ ዘመን መሬትን ወደ ግል እንዲዞር መፍቀድ ማለት እነዚህ ጥቂት የዘመኑ ሰዎች አሁን ከያዙትም በላይ ሰፋፊ መሬቶችን በፍጥነት እንዲያግበሰብሱ ሁኔታዎችን ማመቻቸት ማለት ነው። ዘመነኞቹ “መሬት ወደ ግል ሊዞር ነው” የሚለውን ሲሰሙ፣ በውጭ ባንኮች የከዘኑትን ገንዘብ እያወጡ መሬት በፍጥነት ለመግዛት ይጣደፋሉ። ስርአቱም የተወሰኑ ሰዎች ሰፋፊ መሬቶችን እንዲይዙ ሁኔታውን ያመቻችላቸዋል። ያልተያዙ መሬቶችን ለመግዛት ገንዘብ ቢያጥራቸው እንኳን የባንክ ብድር ይመቻችላቸዋል። የመንግስት ድርጅቶች ወደ ግል ሲዞሩ ያየነው ህገወጥ አሰራር በመሬት ሽያጭ ላይ እንደማይደገም ምንም ማረጋገጫ የለም ። የሻኪሶ ወርቅ ማእድን በስንት ነው የተሸጠው? በርካታ የመንግስት የንግድ ድርጅቶች እንዴት ነው ወደ ግለሰቦች የዞሩት? የተሸጡበት ገንዘብ መጠን ለህዝብ ተነግሮ ያውቃል? ገንዘቡስ መንግስት ካዝና መግባቱ ይታወቃል?
      ቅንጅት አዲስ አበባን ሲያሸንፍ፣ የስርአቱ ልጆች ሰፋፊ መሬቶችን መቀራመት ጀመሩ፣ ኢህአዴግም ሆን ብሎ ሁኔታዎችን አመቻቸላቸው። ኢትዮጵያ በቅኝ ግዛት ስር ያለች ትመስል ነበር። ቅንጅት ቢጨንቀው ” የመሬት ዝርፊያው በአስቸኳይ እንዲቆም” የሚጠይቅ መግለጫ አወጣ። የሚሰማ ግን አልነበረም። አላሙዲ ሳይቀር ጊዮርጊስ መሃል አደባባይ ላይ ለአመታት አጥሮ ያስቀመጠውን ቦታ እንዳልቀማ ብሎ ለመጀመሪያ ጊዜ አረሰው። ከዚያ ወዲህ ድፍን አስር አመት ምንም ስራ አልሰራበትም። ቅንጅት አዲስ አበባን እንደማይረከብ ሲያውቅ፣ ኢህአዴግ በመናኛ ገንዘብ ያዘረፈውን መሬት መልሶ ለመሰብሰብ ተሳነው። መሬት ወደ ግል ሊዞር ነው ቢባል ተመሳሳይ ነገር እንደሚፈጠር አልጠራጠርም።
      በዚህ በዘርና በጥቅም በተማከለ ስርዓት ውስጥ ሆኖ መሬት ወደ ግል ይዙር ብሎ መጠየቅ በራስ ላይ እባብ እንደመጠምጠም ይቆጠራል ። ስለመሬት መሸጥና መለወጥ ለማውራት ኢህአደግ መቃብር እስኪገባ ድረስ መጠበቅ ግድ ይለናል። መታገል ያልብንም ኢህአዴግን ወደ መቃብር ለመሸኘት ነው። በእርሱ መቃብር ላይ አዲስ ስርአት ስንፈጥር ፣ ያን ጊዜ፣ ሁሉንም በማያስደስት ፣ ሁሉንም በማያስከፋ መልኩ መሬት ማከፋፈል ይቻላል።
      ኢህአዴግ እስኪወድቅ መሬት በመንግስት እጅ መሆኑን በጽኑ እደግፋለሁ!
      ( ማሳሰቢያ ይሄ የግል አቋሜ ነው። አንድነት ፓርቲ በቅርቡ
      ካስተዋወቀው የሚሊዮኖች ድምጽ ጋር በፍጹም አይያያዝም። ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ Wealth Over Work- በሚል ርዕስ ፓውል ክሩግማን The New York Times ላይ የጻፈው ጽሁፍ ነው። በዚህ ዙሪያ ሰፊ ክርክር እንደሚኖር እጠብቃለሁ)