Ascent Africa private equity fund eyes $60 million by mid-2015 in Ethiopia

NAIROBI (Reuters) – Private equity firm Ascent Capital wants to increase its east Africa fund to $60 million by mid-2015 from $50 million it has raised so far and plans to announce completion of its first investment in about two weeks, a partner said on Monday. Ascent is one of several private equity firms to

The post Ascent Africa private equity fund eyes $60 million by mid-2015 in Ethiopia appeared first on 6KILO.com.

ይኸ አዲስ ይሆን? ማን ነው ሰላቢው? ማን ነው ጡት ቆራጩ?

image

ይኸ አዲስ ይሆን?
አስፋ ጫቦ

ገነሼ ማዳ የተባለ ሰው፤ጋሞ፤ሆላንድ በትምህርት ላይ ያለ፤ እዚሁ Facebook ላይ ዛሬ ጥዋት የነገረኝን ላካፍል ፈለግሁ። ጋላን/ ኦሮሞን ፤ጋሞ ጌርጌዳ ነው የሚለው አለ። ከዚህም ሌላ ኦቾሎና ዶኮ የጌርጌዳ መቃብር አለ፤ይህም የወረራረው ጦርነት ውጤት ነው የሚል ነው።
ኦቾሎ ማለት ከአርባ ምንጭ ወደጨንቻ ሲወጣ በስተቀኝ አንደ ጉዙፍ ምሰሶ ቆሞ የሚታየው አገር (ዴሬ) ነው። ዶኮ ደጎሞ ከጨንቻ ከተማ ምዕራብ፤ከኤዙሜ ወንዝ ወዲያ የሚታየው አገር(ዴሬ) ነው፤
እኔ ጌርጌዳን አውቃለሁ። የማየውቅ ጋሞ ያለ አይመስለኝም። እስከ 1956 ፤ማለትም ጋንታ ጋሮ የሚባለው ቦታ ህዝቡ ተንቅሎ አርባ ምንጭ ከተማ ከመሆኑ በፊት በየአመቱ መጥተው የሚዘርፉ፤ የሚስልቡ፤እርጉዝ ሴት ሳትቀር ሆድዋን ዘረጥጠው ሽሉን ወንድ ከሆነ የሚስሉቡትን ጉጂውች ጌርጌዳ እንደሚልዋቸው ነው። እንጅ ጌርጌዳ ማለት ጋሞ ጋላን/ ኦሮሞን መጥሪያ ስሙ አድርጌ አልወስደኩም ነበር።
ይህ ከኩሉፎ ወንዝ አርባ ምንጭ ጀምሮ አስከ ጨንቻ መታጥፊያ ያለው የስምጥ ሸለቆ ዘንበል ያለው አባያን የሚነካው ቦታ መሬት ጋንታ ጋሮ፣ሻራጋሮ፤ኦቾሎ ጋሮ ፤ይባላል። ጉጂዎቹ/ ጌርጌዳዎቹ የጋንታንና የሻርን ህዝብ ሲዘርፉም ሲስልቡም የኦቾሎን ህዝብ አይዘርፉም፤ አይስለቡም ይባላል። ለምን? ሲባል ከኦቾሎ ጋር እንዳይነካኩ ዉል ገበተዋል ይላሉ።

ይህ ከሆነ ይህ የሚያመለክተው ጋላ/ ኦሮሞ የወረረው ጊዜ/ወቅት ረዥምና (sustained) ለውል የሚያበቃ፤ የመቃብር ቦታ ሁሉ ለታሪክ የተወ ረዣዝም ጦርነቶች አድረገዋል ማለት ነው። ወይም ሊያሰኝ የሚችል በቂ አቅጣጫ ጠቋሚ የሚታዩ የሚዳሰሱ መርጃዎች አሉ ማለት ነው። የጌርጌዳ ጭፍጨፋን ድንገት አርጅተው ሊሆን ይችላል እንጅ የሚያዉቁ የጋንታ ፤የሻራ ሰዎች ዛሬም በህይወት ይገኛሉ ብየ አምናለሁ።ጋንታ የእናቴ የማቱኬ አገር ስለሆነና ልጅ ሁና ይህንን የጌርጌዳ ዘረፋና ጭፍጨፋና ወረራ የአይን ምስክር ብቻ ሳትሆን ብዙ ዘመዶችዋም ተፈጅተዋል። እኛም ይህንን እየሰማን ነው ያደገነው። የመጨረሻው የጌርጌዳ ስለባ የተፈጸመው በ1970ዎቹ ውስጥ ነበር። አባያ ሀይቅ ዳርቻ የተሰለበው የፖሊስ ባልደረባ ነበር።
ይህ ጋላና ኦሮሞ እያልኩ የተጠቀምኩት ስራዬ ብየ ነው።ጋላ ማለት ኦሮሞን የማከሰስና ዝቅ የማደርጊያ የንቀት ምልከት ነው እየተባለ ይነገራል። ነው እንዴ? እላለሁ።

ዓጼቴዎድሮስ ለንግስት ቪክቶርያ በጻፉት ደብዳቤ “አባቶቼ አምላክን ስለአሳዘኑ ጋላና እስላም ስደደባቸው” ይላሉ ዓጼ ቴዎድሮስ ጋላን ለማንኳሰስ ብለው ነው ጋላ ያሉት? ከዚያ በፊት የማያውቁትን ሕዝብ እንዴት ለምንስ ያንኳስሳሉ? ይንቃሉ? ዝቅ አድርገዋቸው አይተዋቸው ነው እንዳይባል ይኸው በጦርነት አሸንፈው “ያባቶቼ አገር” የሚሉትን ወስደውባቸዋል። ከዚህም ሌላ እኔው ራሴ በተዘዋወርኩባቸው የኦሮም አካባቢዎች አጋጣሚው ሲገኝ “አሁን ጋላ ብል መዝለፌ ነው!” ብየ እጠይቃለሁ። “ብትፈልግ ኦሮሞ ብትፈልግ ጋላ ልትል ትችላለህ!” የሚል መልስ በጠይኩ ቁጠር አገኛለሁ። የሚታየኝ ከዚህ ውስጥ የፖለቲካ ትኩሳቱን አውጥተን የዚህ ጋላ የሚለው ቃል ታሪካዊውና እርግጠኛ ምንጩ ምንና ከየት እንደሆነ ብናውቅ ምስሉን ሙሉ የሚያደርገው ይመስለኛል።
አንድ ሌላ ነገር ፤ ዶኮ ከበርብር ግፋ ቢል የ3 ስአት መንገድ ነው። ኦቾሎ ደግሞ ግፋ ቢል የ4 ሰአት መንገድ ነው። ብርብር ማለት አባ ባህርይ ዜናሁ ለጋላን የጻፉበት የብርበር ማርያም ያለችበት ባለፈው በዩሱፍ ያሲን መጽሐፍ ግምገማ ያነሳሁት ነው።ይኸ ከሆነ አባ ባህርይ የሰሚ-ሰሚ ሳይሆን ለጋላ ወረራ የዐይን ምስክር ሳይሆኑም አይቀሩም ወደሚል አስተያየት የሚወስደን ይመስላል።
ይህንን ነገር ለወዳጄ ፤ለዜናሁ ለጋላ ተርጓሚ ዶክተር ጌታቸው ኃይሌ ልነግረው ፈልጌ ስልኩም አልስራ አለኝ፤ በemail አልመልስልኝ አለ። ያኔ፣ ዜናሁ ለጋላን ያሳተመ ስሞን የብርብር ማርያምን ፎቶግራፍ ልኬለት “ምነዉ ምነው አስፋ መጽሐፉ ከመታተሙ በፊት ብትልክልኝ ሽፋን የማደገውን” ብሎ አዘነብኝ። አሁን ደግሞ በዚህም ሳያዝንብኝ የሚቀር አይመስለኝም። ከኔ የተሻለ ግኑኝነት ያላችሁ ብትነግሩት ደስታውንም አልችለውም።
ሌላ፤ ፊንፊኔ ከሚባል የኦሮሞ ራዲዮ ጣቢያ ጋርም የ2.30 ሰአት ያክል ቃለ ምልልስ አድርጌ ነበር። ኦሮሞ አዲሳባን ፍንፍኔ ይላል። ዕቴጌ ጣይቱ ደግሞ አዲስ አበባ አሉ። ጋሞ ደግሞ ቱንጋ ይላል።ቱንጋ ጥንት የጋሞ ዴሬ ነበር? 

ፊንፊኔ ራዲዮ እዚያ ተቀባይነቱ ጥሩ ሆኖ ተጨማሪ ብዙ ዘለፋ፤ ብዙ ትኩሳት ያለው ቃላት፤ ብዙ አርፋም ደፍቋል።Facebook ላይ የሰማሁትን ነዉ።ሁሉንም እቀበላለሁ።ሌላ ቦታ እንዳልኩት “አስፋ አደባባይ ውጣ፤ጻፍ ፤ተናገር፤ተናዘዝ!” ብሎ ያስገደደኝ ሰው የለም። ወድጄ ያደርግኩጉት ነውና ምርቱን እንዳለ እቀበላልሁ። ሌላ ቦታ እንዳልኩት ያሜሪካው ፕረሲዳንት የነበረው ትሩማን እንዳለው ወይም ብሏል እንደተባለው ነው:: If You Can’t Stand the Heat Get Out of the Kitchen” “ሙቀቱን፤ጢሱን የማትቋቋም ከሆነ ከማድቤቱ ውጣ!” እኔ ከዚህ ከኢትዮጵያ ማድቤት የምወጣ መስሎ አይታየኝም። ከሸጋው፤ከመጥፎውም ሆነ ከጥፉው። ያው እንደማንኛቸውም አገር በየአይነቱተሰጥቶናልና! ይልቁንም ከዚህ ታሪካዊ አዲስ ግኝት፤ከጢሱም ፤ከአረፋዉም ተጨማምቆ የተሻለ፤የሚያምር፤የሚበጅ ኢትዮጵያን ልናመጣ እንችላለን ብዬ አምማናለሁ!! አሰፋ ከሚደደፍቀዉ አረፋም የሚገኝ አለ ብሏል እንዳትትሉኝ! አረፋ ያፀዳል! ነዉ ያልኩት:: Yes! We Can!! ነው የሚሉት
አዎን !!እንችላለን!!

የ‹አማራ›ና ‹ቅማንት› ጉዳይ

በ ሙሉቀን ተሰፋው

የ‹አማራ›ና ‹ቅማንት› ጉዳይ
=====================

ይህን ጉዳይ ስሸሸዉ የቆየሁት ነገር ነዉ፡፡ እርግጥ አንድ ጊዜ ፋክት መጽሄት ላይ ነካክቸዉ ነበር (ያኔ ኤዲት ሲደረግ የኔን ሀሳብ ሙሉ በሙሉ ይዞ ባይወጣም) ግን እስከ መቼ እየሸሸሁትስ እዘልቃለሁ? የማያስኬድ ነገር ሲሆንብኝ ይህን ሀሳብ ለመሞነጫጨር ተገደድኩ፡፡ ያለዉን ነበራዊ ሁኔታ በዚህ መልኩ ማስቀመጡ ጠቀሜታም ጉዳትም ይኖረዋል፡፡
ጉዳቱ አንዳንድ የአስተሳሰብ ስንኩላን ከእሳቱ ላይ ቤንዚን ሊጨምሩ ይችላሉ፡፡ በሌላ መልኩ ጠቀሜታዉ ደግሞ የህብረተሰቡን ንቃተ ህሊና በመጨመር እየተፈጠረ ላለዉ ሁናቴ መፍትሄ ሊያፈላልጉ የሚችሉ ግለሰቦችና ምሁራን አይጠፉም፡፡ ጥቅሙንም ጉዳቱንም በመመዘን ለአንባቢያን ማሳወቁ ይጠቅማል ብየ ስላሰብኩ በሚከተለዉ መልኩ አስቀምጨዋለሁ፡፡
የዛሬ ወር አካባቢ መሆኑ ነዉ፡፡ ከአዘዞ አጼ ቴዎድሮስ አዉሮፕላን ማረፊያ ወደ ፒያሳ አንዲት ቢጫ ታክሲ ኮንትራት ይዣለሁ፡፡ የታክሲዉ አሽከርካሪ ደስተኛ አለመሆኑ ፊቱ ቢመሰክርም ምን እንደሆነ መጠየቅ አልፈለግኩም፡፡ ግን በራሱ ጊዜ የሆነዉን ነገረኝ፡፡
እድሜዎ በአርባዎቹ መካከል የሚገኘዉ የታክሲ አሽከርካሪ ያስከፋዉ ነገር ሚስቱንና የልጆቹን እናት ያጣበት ምክንያት ነዉ፡፡ ‹‹አስራ ሰባት (17) አመታት ከሚስቴ ጋር አብረን ስንኖር ስለ እርሷ ዜግነት(?) የማዉቀው ነገር አልነበረኝም፡፡ ሰዉነቷ ብቻ በቂዬ ነበር፡፡ እዉነቴን ነዉ የምልህ የጎንደር ልጅ ከመሆኗ ዉጭ የማዉቀው አልነበረኝም፡፡ በጋብቻችን ለአቻዎቻችን አርኣያ የምንሆን ነበርን፡፡ በትዳራችን 3 ልጆችን አፍርተናል፡፡ የመጀመሪያዋ 16 አመቷ ነዉ፡፡ ባለፈዉ የጥቅምት መድሀኒዓለም እናቷ ደወለችልኝና ለመድሀኒዓልም ዝክር ዝግጅት ታግዘኝ ላካት አለችኝ፡፡ እኔም በደስታ እናቷን እንድታግዝ መሄዷን በደስታ ተቀበልኩ፡፡ የጥቅምት መድሀኒዓለም አልፎ ግን ከነገ ዛሬ ትመጣለች እያልኩ ከልጆቼ ጋር ብናያት የዉሃ ሽታ ሆነች፡፡ ስልክ ስንደዉል ስልኳን ዘግታለች፡፡ መጨረሻ ቤተሰቦቿ ካሉበት ቦታ ትክል ድንጋይ ሰዉ ተላከ፡፡
‹‹ልጃችን ‹አማራ› አግብታ አትኖርም! የሚል መልስ ከእናቷ ሰሙ የተላኩት ሰዎች፡፡ ሶሰት አመት ያልሞላዉን ህጻን ልጅ እና ሌሎቹንም ልጆቿን ትታ ለመቅረት እንደወሰነች ሰማሁ፡፡ በቄስ በሽማግሌ አስጠየቅኳት፡፡ ወይ ፍንክች የአባ ቢለዋ ልጅ! ልጆቼ ሲያድጉ ሰራተኛ አላያቸዉም፡፡ ሙሉ በሙሉ የሚያስፈልጋቸዉን ሁሉ እርሷ እና እኔ ነን የምናሟላቸዉ፡፡ ሰራተኛ አሁን አስገብቼ ለትምህርት ቤት ምሳ እንድትቋጥር ሳደርግ ልጆቹ ሳይበሉት እየተመለሱ እርሃብ ሊገድላቸዉ ሆነ፡፡ አሁን የቤቱንም የዉጩንም ስራ ብቻየን ይዠዋለሁ›› በማለት ልብን የሚሰብረዉን ግለ ታሪክ አጫወተኝ፡፡
ሌላዉ አጋጣሚ ደግሞ እንደዚህ ነዉ፡፡ በህዝብ ትራንስፖርት ወገራ አዉራጫ ዉስጥ ኮሶዬ ከሚባል ቦታ ደርሼ ለመምጣት ተሳፈርኩ፡፡ መኪና ውስጥ ከፖለቲካ ዉጭ የሚወራ ወሬ መጥፋቱን አስተዋልኩ፡፡ በቃ ግማሹ መንግስትን ተቃዉሞ ከፊሉ ደግሞ መነታረክ ነዉ፡፡ ስሄድ ምንም ሳልናገር ደረስኩ፡፡ ስመለስም ሌላ የፖለቲካ ንትርክ ካለባት ሚኒባስ ውስጥ ገባሁ፡፡ እርግጠኛ ነኝ- የፓርላማ ሰዎች ያን ያክል ውይይት አያደርጉም፡፡ ወደ ጎንደር ከተማ ስንቃረብ ግን ፖለቲካዉ ‹ቅማንት- አማራ› ሆነ፡፡ አንድ መሀል ሰፋሪ ወጣት ነገሩን አቀጣጠለዉ፡፡
ከአምባ ጊዎርጊስ የተሳፈረ ግለሰብ ሸምበቂት ከምትባል አነስተኛ መንደር ሲወርድ ‹አቀጣጣዩን› ልጅ ‹ቅማንት ስለሆንክ እወድሀለሁ!› ብሎት ወረደ፡፡ ግራ ገባኝ፡፡ ይህ ጎጠኝነት ገበሬዉ ድረስ ስር መስደዱ አሳዘነኝም አንገበገበኝም፡፡ ከደቂቃዎች በኋላ ከጀርባየ ካለዉ ወንበር የተቀመጡት ሁለት ሰዎች ሊደባደቡ ሲታገሉ ዞርኩ፡፡ መኪናው ቆሞ ሰዎቹን መገላገል ያዝን፡፡
ከአፍታ በፊት በወዳችነት ሲያወሩ የነበሩት ግለሰቦች ለምን እንደተጣሉ አጣራንና የበለጠ አዘንን፡፡ ሊደባደብ የሚገለገለዉ ሰዉዬ ‹እኔ በአባቴ ቅማንት ነኝ፡፡ እርሱም ቅማንት ነዉ፡፡ የሚኖረዉ ጎንደር ዙሪያ ሆኖ ሳለ እባክህ በእናንተ አካባቢ ‹ኮሶየ› ምሽት ፈልግልኝ አለኝ፡፡ ጎንደር ዙሩያ ጠፍቶ ነዉ ኮሶየ ድረስ ምሽት ፍለጋ የምትመጣዉ? ስለዉ ከዚህማ ሁሉም አማራ ሆነብኝ፡፡ ቅማንት ከእናንተ አካባቢ ብዙ አለ ብየ እኮ ነዉ ይለኛል፡፡ አማራ ቢሆኑ ምን ችግር አለዉ? ብየ ስመልስለት ‹ደሞ ከነዚህ ‹እንትኖች› ጋር ነዉ የምጋባዉ? ሲለኝ ስሜቴን መቆጣጠር አቃተኝ!›› በማለት ሲያብራራ እኔ የምናገረዉ ስላልነበረኝ ዝም አልኩ፡፡ አብረዉ የነበሩ ሊደባደቡም የከጀሉ፣ የተጨቃጨቁም፣ ብዙ ያወሩም አሉ፡፡
የተሳደበዉ ግለሰብ ዝምታን መርጧል፡፡ ጥፋተኛነቱን ያመነ ይመስል ነበር፡፡
ግን ከዚህ ሁሉ ምን እንመለከታለን? ዘረኝነትና ጎጠኝነት ገጠር ካልተማረው ማህበረሰብ ድረስ ገብቷል፡፡ በአርማጭሆ፣ ወገራና መተማ በዚህ አመት ብቻ በርካታ ጥንዶች ትዳራቸዉን አፍርሰዋል፡፡ ልጆቻቸዉን በትነዋል፡፡ በሰሜን ጎንደር ዞን ያሉ ፍርድ ቤቶች በዚህ አመት ያስተናገዱት የፍች ጥያቄ ከዚህ በፊት ካለዉ ዘመን ጋር የሚነጻጸር አይደለም፡፡
ለእኔ እስከሚገባኝ ቅማንትና አማራ መካከል ምንም ልዩነት አላየሁም፡፡ የሚኖረበት ቦታ፣ የሚናገሩት ቋንቋ፣ የሚያመልኩት ሀይማኖት፣ የሚመገቡት…. ሁሉ ተመሳስሎ ሳለ ለምን ግን መለያየት አስፈለገ? የ‹ቅማንት ብሄረሰብ› አለባቸዉ በተባሉ ቦታዎች ሁሉ ዞሬ ለመታዘብ እንደቻልኩት ከ‹አማራዉ› የተለየ ቋንቋና ባህል አልገጠመኝም፡፡ ይህ መሬት ላይ ያለ እዉነታ ነዉ፡፡ ቅማንት የሚባል ቋንቋ ነበር፡፡ አሁንም በእድሜ ገፋ ያሉ ሰዎች እንችላለን ያሉኝ አሉ፡፡ አባ ወንበሩ መርሻ (የቅማንት መሪ) ከመሞታዉ በፊት ይህን ጉዳይ አረጋግጠዉልኛል፡፡
በእኔ እምነት ይህ ቋንቋ ፈጽሞ ከመጥፋቱ በፊት ዩንቨርሲቲዎቻችን (በተለይም የጎንደር ዩንቨርሲቲ) መዝገበ ቃላትና ሰዋሰዉን ማስቀረት አለባቸዉ፡፡ ፈቃደኛ የሖኑ ሰዎችም ሊማሩበት ይችላሉ፡፡ ነገር ግን ይህ መሰረታዊ እዉነታ መሬት ላይ ባለበት መልኩ እርስ በራስ ቅራኔ ውስጥ መግባቱ እጅግ አስቀያሚና ኋላ ቀር የሆነ አስተሳሰብ ነዉ፡

Sisi Goes to Addis Ababa

By ALEX DE WAAL, NYTimes Credit Anthony Russo On one of the last occasions an Egyptian president visited Addis Ababa, he got no further than the road from the airport: In 1995 the motorcade of President Hosni Mubarak came under fire from Egyptian jihadists. Mr. Mubarak was saved by his bulletproof car, his driver’s skill and

The post Sisi Goes to Addis Ababa appeared first on 6KILO.com.

Sisi Goes to Addis Ababa

By ALEX DE WAAL, NYTimes Credit Anthony Russo On one of the last occasions an Egyptian president visited Addis Ababa, he got no further than the road from the airport: In 1995 the motorcade of President Hosni Mubarak came under fire from Egyptian jihadists. Mr. Mubarak was saved by his bulletproof car, his driver’s skill and

The post Sisi Goes to Addis Ababa appeared first on 6KILO.com.

Akon: ‘America was never built for black people’

Artist Akon talks about being an African in the US TALK TO AL JAZEERA The Senegalese-American recording artist talks frankly about US race relations, “rebranding” Africa, and his music. Senegalese-American artist Akon is a five-time Grammy nominee who has sold over 35 million records worldwide, and has collaborated with some of the biggest names in

The post Akon: ‘America was never built for black people’ appeared first on 6KILO.com.

Canada’s Prime minister urged to intervene as Canadian languishes in Ethiopian prison

Supporters of Bashir Makhtal say prime minister must negotiate directly to free Makhtal, who has been jailed for eight Debra Black years. IMMIGRATION REPORTER As the eighth anniversary of the rendition and imprisonment of Canadian citizen Bashir Makhtal passes virtually unnoticed, his family members, supporters and Amnesty International are begging Prime Minister Stephen Harper to

The post Canada’s Prime minister urged to intervene as Canadian languishes in Ethiopian prison appeared first on 6KILO.com.

UK diplomats clash over British man on death row in Ethiopia

Officials’ fury after Foreign Secretary claims he couldn’t ‘find time’ to help father-of-three facing execution By Ian Birrell for The Mail online Andargachew Tsege was snatched by officials at Yemen airport last June The 59-year-old was transferred to Ethiopia where he is thought to remain Father-of-three moved to London in 1979 from native African country

The post UK diplomats clash over British man on death row in Ethiopia appeared first on 6KILO.com.

‘Ethiopia’s media crackdown is bad news for Africa’

By Simon Allison, Guardian Without a free press in Addis Ababa, Africans are being locked out of the important decisions being made in their de facto capital, writes Simon Allison It’s not easy being a journalist in Ethiopia. In fact, it’s nearly impossible, according to a new 76-page Human Rights Watch report that documents the

The post ‘Ethiopia’s media crackdown is bad news for Africa’ appeared first on 6KILO.com.