2015 Border demarcation between Sudan and Ethiopia to resume next December

(KHARTOUM) – Ethiopia’s Prime Minister Hailemariam Desalegn said that redrawing the borders between Sudan and Ethiopia will begin next month according to a previous agreement with Sudan’s President Omer al-Bashir. Sudanese president Omer Al- Bashir and Ethiopian prime minister Hailemariam Desalegn sign a series of joint cooperation agreements in Khartoum 4 December 2013 (Photo SUNA)

The post 2015
Border demarcation between Sudan and Ethiopia to resume next December
appeared first on 6KILO.com.

Ethiopian Gunmen Kidnap 5 Sudanese And Seek Ransom Near Gonder

BASANDA- Ethiopian gunmen kidnapped five people in eastern Sudan’s El Gedaref state on Sunday. The chairman of the legislative council of Basanda locality told Radio Dabanga that five herders and farmers were abducted in the areas of Atarab and Tegelein on Sunday. The gunmen contacted their families and demanded a ransom for their release. The

The post Ethiopian Gunmen Kidnap 5 Sudanese And Seek Ransom Near Gonder appeared first on 6KILO.com.

መሣፍንት ባዘዘው: ጎንደሬ አድምጥ!

ጎንደሬ አድምጥ!
(መሣፍንት ባዘዘው)ዛሬ ልወርድብህ ነው! ከዛ መሃል ፒያሳ ላይ ከቆመው የመይሳው ሃውልት ላይ ተለጥፈህ ፎቶ መነሳትህን ተው!! ለጊዜው የቴዲ ልጅ ነኝ እያልክ መዝፈኑንም ያዝ አድርገው።ጀግና ሳንሆን የጀግና ልጅ ነኝ እያሉ መኮፈስ ይብቃን!! የቴዎዽሮስ ሃሞት እንጥፍጣፊዋ እንኳ ከኛ ዘንድ ሳትኖር እንዴት የጀገናውን ስም በከንቱ እንጠራዋለን?

ወልቃይት ሲቆረስ ዝም! ጠገዴ ሲቆረስ ዝም! ዋልድባ ሲታረስ ዝም! አርማጭሆ ሲሸጥ ዝም! የቴዎድሮስ ሃገር ቋራ ሲሸጥ ዝም! ትውልድ በጫት ሱስ እዬደነዘዘ ፣ የትምህርት ፖሊሲው ጥራት እያሽቆለቆለ… እያዬህ “እምቢ!” ማለት ካቃተህ የቴዎድሮስ ልጅ ነኝ አትበለኝ። አሁንስ በዛ ብለህ መነሳት ከቃተህ …እንኳን ከመይሣው ሃውልት ላይ ፎቶ ልትነሳ ነው እና በአጠገቡ ማለፍ የለብህም። እውነት እኔ እዛ ሃውልት ላይ ተደግፌ ፎቶ መነሳት አፍራለሁ። ሌላውን ሁሉ ተወው! እስኪ የወያኔን ሃሳብ ከመደገፍ ተቆጠብ።እስኪ መጀመሪያ በሃሳብ ደረጃ “እምቢ!” በል!

እስኪ ግራ እና ቀኝህን ተመልከት! ያቺ የተቀደሰች ከተማ በጫት ቤቶች ስትሞላ እየታዬህ አይደለም?ትንንሾችህ በአንተ እግር እዬተተኩ ወደ ሱስ እዬገቡ እንደሆን አስተውለሃል? ከ20 አመት በፊት የነበሩት ቸቸላ ሆስፒታል እና ፖሊ ክሊኒክ ስንት ሆስፒታል እና ክሊኒክ ተጨመረላቸው? ወገንህን እሲኪ ቸቸላ ላይ ሄደህ እየው…ሜዳ ላይ እንደ ምናምንቴ ወዳድቆልሃል!ፋሲለደስ ስንት ሃይድኩል ወለደ? ምንም!! ስንት ፋብሪካ ተተከለ? …… የወያኔን ሴራ ከአንተ የበለጠ ማን ያውቀዋል? እና ምነው ተኛህ? ኧረ ንቃ!!!

በእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ እዬተቧደንክ ከመነታረክ እስኪ ስለ ቴዎድሮስ መንፈስ ተወያይ። እውነት የቴዎድሮስ ልጅ መሆናችንን በተግባር እናሳይ!! ዘፈን ብቻ ሰለቸኝ!! የኛም ትውልድ ቴዲን አምጦ ይውለድ እና መጭው ትውልድ ይዝፈንልን!! በየመጠጥ ቤቱ የአራዳ ልጅ፣ የፒያሳ ልጅ እያልክ በቢራ ጠርሙስ ስትፈነካከት ለም መሬትህ ለሱዳን ተቸብችቦ አለቀልህ…እስኪ በየቀበሌ መቧደንክን ትተህ አንድ ሁን እና በጠላትህ በወያኔ ላይ ተነስ!!

የተዋበች የምንተዋብ ፣የጥሃይቱ ሴት ልጆች በየሺሻ ቤቱ ሲውሉ እያዬህ እንዴት አስቻለህ? ከትንንሽ እህቶችህ ጋር የሺሻ ገመድ እዬተቀባበልክ ስታጨስ ምንም አይሰማህም?? ኧረ እንደተኛን ነግቶ ተመልሶ መሸ………

አስገድዶ መድፈር በጎንደር ዩኒቨርሲቲ

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአምስት ዓመታት በፊት በመምህሯ መደፈሯ የተገለፀ አንዲት ተማሪ ሁኔታዉን ለሚመለከተዉ አካል አቤት ብትልም እስካሁን መፍትሄ አማግኘቷ አነጋጋሪ እንደሆነ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል።

ጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከአምስት ዓመታት በፊት በመምህሯ መደፈሯ የተገለፀ አንዲት ተማሪ ሁኔታዉን ለሚመለከተዉ አካል አቤት ብትልም እስካሁን መፍትሄ አማግኘቷ አነጋጋሪ እንደሆነ የደረሰን ዘገባ ያመለክታል። በዩኒቨርሲቲዉ የተማሪዎች አገልግሎት ዲን ተፈፀመ የተባለዉን አስገድዶ የመድፈር ወንጀል ጥርጣሬ ደብዛ ለማጥፋት ተጎጂዋ ሃኪም ቤት የታከመችበትን ማስረጃ ምግኘት እንዳልቻሉ አንድ ስማቸዉ እንዳይገለጽ የጠየቁ የሰብዓዊ መብቶች ተሟጋች ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል።

http://www.dw.de/%E1%8A%A0%E1%88%B5%E1%8C%88%E1%8B%B5%E1%8B%B6-%E1%88%98%E1%8B%B5%E1%8D%88%E1%88%AD-%E1%89%A0%E1%8C%8E%E1%8A%95%E1%8B%B0%E1%88%AD-%E1%8B%A9%E1%8A%92%E1%89%A8%E1%88%AD%E1%88%B2%E1%89%B2/a-16481900