በቋራ ያሉ የናይጄሪያ ዘላኖችና ‹ሸውሽዌ› ክፍል ፪

By Muluken Tesfaw

በቋራ ያሉ የናይጄሪያ ዘላኖችና ‹ሸውሽዌ›

ክፍል ፪

በዚህ በርሃና ጫካ ብዙ ገራሚ ነገሮች አሉ፡፡ መንደሮች በድንገት በሚነሳ ቋያ ሙሉ በሙሉ ይድማሉ፡፡ በርሜልን ጨምሮ ብዙዎቹ የሰፈራ መንደሮች በበርሃ ቋያ በየጊዜው እየወደሙ እንደገና ይሰራሉ፡፡ የበርሃ ሰው ተስፋ አይቆርጥም፤ ነገ በቋያ ቤቱ እንደሚወድምበት እያወቀ እንደገና ይገነባል፤ ይቃጠልበታል፤ ይሰራል…

በየመንገዱ ጅራታቸው የውሻ ያክል የረዘመ በጎች በብዛት አሉ፡፡ እነዚህ በጎች ‹ፈላታ› በመባል ይታወቃሉ፡፡ ፈላታዎች የናይጀሪያ ዘላኖች በጎች ናቸው፡፡ በጎቹ በዘላኖቹ ስም ፈላታ እየተባሉ ይጠራሉ፡፡ የናይጀሪያ ዘላኖች የሱዳንና የቻድን መሬት አልፈው ለምን ቋራ እንደከተሙ ለኔ ብዙ እንቆቅልሽ ነው፡፡ ነገር ግን ቋረኞች እንደሚሉት በቋራ ጫካዎች ውስጥ ፈላታዎች ከብቶቻቸውንና በጎቻቸውን ያረባሉ፡፡ እርግጥ ነው አካባቢው የግጦሽ ሳርና ውኃ ችግር ስለሌለበት ለከበት አርቢዎች ምቹ ቦታ ነው፡፡ የፈላታ ከብቶች አውሬዎች ናቸው፡፡ አበሻ ካዩ አባርረው ይዋጋሉ፡፡ ብዙ ግዜ አበሻዎች ከዛፍ ካልወጡ በስተቀር አያመልጧቸውም፡፡ ነገር ግን አበሾች የፈለታዎችን ከብቶች በጥይት በመምታት እንደሚወስዱባቸው ሰምቻለሁ፡፡ የፈላታ በጎች ተራብተው በድፍን ቋራና መተማ በብዛት አሉ፡፡ መልካቸው ነጫጭ ሲሆን ጸጉር የላቸውም፡፡ ጅራታቸው ረጅም ነው፡፡ ሥጋቸው ቆንጆ ነው ሲሉ ሰምቻለሁ፡፡ እርግጥ ነው የሔድኩበት ቀን አርብ በመሆኑ የበግ ሥጋ አልበላሁም፡፡

ወደ ጫካ አንድ ሰው ጂፒኤስ ሳይዝ ከሔደ የመጥፋት እድሉ ከፍተኛ ነው፡፡ በተለይ ደግሞ አዲስ የመጣ የመንግሥት ተቀጣሪ ከሆነ መስክ ብቻውን መሔድ የለበትም ይላሉ፡፡ ወደ ጫካው ከሔደ በኋላ በርሃው ሕሊናውን ያነሆልለዋል፡፡ በበርሃ ሕሊናን የመሳት ሒደት ‹ሽውሽዌ› ይባላል፡፡ ሽውሽዌ የያዘው ሰው አቅሉን ስቶ ከመጓዝ ውጭ ወደየትና እንዴት እንደሚሔድ አያውቅም፡፡ በዚህ በርካታ ሰዎች ጠፍተው ቀርተዋል አሉ፡፡ ‹አሉ› የምለው ሰዎች በነገሩኝ መሠረት ስለምነግራችሁ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ይህች ሽሽዌ የምትባል ‹ነገር› አንዳች መለኮታዊ ነገር ይኑራት አይኑራት የሚታወቅ ነገር ያለ አይመስለኝም፡፡ እርግጥ ብዙ ሰዎች እንደ ሰይጣናዊ ሥራ የሚቆጥሩት አሉ፡፡ አንዳንዶች ደግሞ የአየር ንብረቱ ሞቃታማ መሆን የሰውነታችን ሥነ ሕይወታዊ (ፊዚዎሎጅካል) ሥራ ስለሚያወከው አእምሯችን በአግባቡ ሥራውን ማከናወን ያቅተዋል፡፡ በዚህም አቅጣጫ የመለየት ችግር ይገጥመናል የሚሉ አሉ፡፡ ነገር ግን የትኛው ትክክል እንደሆነ የተሰራ ጥናት አላየሁም፡፡ አቅጣጫ ሲጠፋ በአካባቢው የሚኖሩት ጉምዞች አቅጣጫን ለማወቅ የሚሆናቸው የለም፡፡ አንድ ጊዜ እንዲህ ሆነ አሉ፡፡ አንዲት ግብርና ተመድባ የመጣች ሴት ወደ ጫካው የገጠር አካባቢ ትሔዳለች፡፡ ብዙ እንደተጓዘችም ሽውሽዌ ትይዛታለች፡፡ ያኔ ወደየት እንደምትሔድ ሳታውቅ ብዙ ከገለጎ (የወረዳው ከተማ) ርቃ ሒዳለች፡፡ በዚህም ከፈላታዎች እጅ ትገባለች፡፡ እንደነገሩኝ ከሆነ ይህች ልጅ ፈላታዎችን አግብታ እርሷም ዘላን ሆና በመኖር ላይ ነች፡፡

ፈላታዎች ሴቶችን ጠልፈው ወይም ሽውሽዌ ከወሰደላቸው መቼም አይለቁም፡፡ በዚህ የተነሳ ይህች ሴት አንዳንዴ ለዘመዶቿ ደብዳቤ ከመጻፍ የዘለለ ከጫካ ውጭ ያለውን ዓለም በሽውሽዌ ከተጠለፈችበት ጊዜ ጀምሮ አይታው አታውቅም፡፡ ለማምለጥ ብትሞክር በፈላታዎች ጥቃት ስለሚደርስባት አስባም የምታውቅ አይመስልም፡፡ ፈላታዎች ብዙም ልብስ መልበስ የለመዱ አይደሉም፡፡ በሬዎቻቸውም ሆነ እነርሱ የማሽተት ኃይላቸው ከፍተኛ እንደሆነ ይነገራል፡፡ አደጋ ከመጣባቸው አሊያም አበሻ እየቀረባቸው መሆኑን ከብዙ ኪሎ ሜትሮች ርቀት አውቀው ይርቃሉ፡፡ እነዚህ ሰዎች አእዋፍም የሚታዘዟቸው ይመስላል፡፡ ወደ እነርሱ እየቀረበ ያለው ሰው ይሁን ሌላ አንበሳ ሁሉንም አእዋፍ ሊነግሯቸው እንደሚችል የወሬ ምንጮቼ ያረጋግጣሉ፡፡

የአካባቢውን ማኅበረሰብ ወባ፣ እባብና ሽውሸዌ ያጠቁታል፡፡ መርዛማ የበርሃ እባብ አለ፡፡ በእጽ የሚከላከሉት ሰዎችም አሉ፡፡ እርግጥ እባብ የሚከላከሉበት እጽ ከሱዳን አስማተኞች የተገኘ ነው አሉ፡፡ አዲስ አበባ እባብ ስለሌለ ጥበቡን ማወቅ እንጅ እጹን አልፈለግኩትም፡፡ ስለዚህ ይዤ አልተመለስኩም፡፡ ጥበቡንም አልቀሰምኩም፡፡ ደሞስ መሥራት አለመሥራቱን ሳላረጋግጥ እንደኔ ዓይነት ቶማስ (ተጠራጣሪ) እንዴት ይዞ ይመጣል? ሽውሽዌ ብዙ ሰው ታጠቃለች፡፡ አንድ ጊዜም እንዲሁ ከቋራ ወረዳ ወደ ገጠር የተላኩ አምስት ያክል ባለሙያዎች በሽውሽዌ ይጠቃሉ፡፡ ሕሊናቸው ነሁልሎ የሚሔዱበትን አቅጣጫ ሳቱ፡፡ ሽውሽዌ የተጠቃ ሰው ያለ አቅጣጫው ኃይሉ እስከሚያልቅ ድረስ መጓዝ ነው፡፡ የእነዚህ ባለሙያዎች ኃይል አልቆ ኖሮ ወደቁ፡፡ ወዳጆቻቸው ለመፈለግ ሞከሩ፡፡ ሊገኙ አልቻሉም፡፡ ከረጅም ጊዜ በኋላ ለሌላ መስክ (ፊልድ) የተላኩ ሰዎች በርሃ ውስጥ ወዳድቀው በክረምት ዝናብ ሣር በቅሎባቸው ተገኘ አሉ፡፡ እንግዲህ ስለ ሸውሸዌና ፈላታ ናይጀሪያውያን ካላይ ያወጋሁት በሙሉ በቋረኞች በተነገረኝ መሠረት እንጅ ከፈለታ በግ ውጭ ያየሁት አንድም ነገር የለም፡፡ እርግጥ ነው ሁሉምን ለማየት አይቻለም፡፡ ደግሞም አደገኞች ናቸው፡፡ ሽውሽዌን ልይ ብል ተመልሦ ይህን ሪፖርት ማን ያስነብባችኋል? ዘላኖቹንም ማግኘት ሌላው ከባድ ነገር ነው፤ ደግሞም የሚመጡበት ወቅት አላቸው እንጅ ዓመቱን በሙሉ አይኖሩም፡፡ እባብ እንኳን በእውን በናሽናል ጂኦግራፊ ሳየውም ውቃቢየ አይወደው፡፡ በወባ ለመለከፍ አንድ ቀን ማደር ይጠበቅብኛል፡፡ ሁሉንም ግን አልሻም፡፡ የሔድኩባት ፒክ አፕ ወደ ሸኽዲ ትመለሳች፡፡

ጊዜ ቢኖረኝ ኖሮ ብዙ ነገር የሚታይ ነበር፡፡ ወደ ደጋማው የቋራ አካባቢ ቴዎድሮስ ከተማ የሚባል አለ፡፡ እዚያ የአጼ ቴዎድሮስ የልጅ ልጆችና ዘሮች እንዳሉ ሰምቻለሁ፡፡ እነርሱን የማግኘት እቅድ ነበረኝ፡፡ ጊዜም ገንዘብም ስለተመናመነ ብሎም ቀጣይ ጉዞ ስላለብኝ ያን በርሃ ትቼው መመለስ ግድ ይላል፡፡ ወጣሁም፡፡ ሸኽዲ ከተማ ባጃጅ ውስጥ ያነበብኩት ጥቅስ ለአካባቢ ምቹ (ኢንቫሮንመንት ፍሬንድሊ) ነው፡፡ እንደ አዲስ አበባ ‹የሰው ትርፍ የለውም› የሚል ጥቅስ እዚህ ቦታ አይታሰብም፡፡ ትርፍ አትጫን የሚል ሕግ የለምና፡፡ ባጃጅ ውስጥ ያለው ጥቅስ ‹ጊዜን አይቶ የማይከዳ ዕውነተኛ ጓደኛ የበርሃ ጥላ ነው› ይላል፡፡ ከዚህ የበለጠ ዕውነት በዚህ አካባቢ የለም፡፡ ቀን ላይ አይቸዋለሁና፡፡

አሁን እየመሸ ነው፡፡ ጀምበር መዘቅዘቅ ጀምራለች፡፡ ወደ ጎንደር የሚሔዱ መኪናዎችም ብዙ የሉም፡፡ ወደፊት 161 ኪሎ ሜትር መጓዝ ይጠበቅብኛል፡፡ ያገኘዋት ሚኒ ባስ በዚያ ሙቀት ሰው ጥቅጥቅ አድርጋ ሞላች፡፡ ጋቢና ነበርኩ፡፡ ጋቢና ሾፌሩን ሳይጨምር ሦስተኛ ሰው ታከለልን፡፡ አይሆንም ማለት አይቻልም፡፡ ዝም ብሎ መጓዝ ነው፡፡ ገንዳ ውኃን አለፈን፤ ደረቅ አባይ፤ ነጋዴ ባህር፤ አርሴማ፣ ሰራባ፣ ጭልጋ…. ጎንደር ምሽት ሦስት ሠዓት ሲሆን፡፡ ነገ ቀጣይ ጉዞ አለ፡፡ ወደ አርማጭሆ፡፡

በላንድ ማርክ ሆቴል የተደረገው የወልቃይት ጉዳይ ስብሰባ

የአርማጭሆን ጉዞ ከመጀመራችን በፊት ግን ትናንት በጎንደር ላንድ ማርክ ሆቴል ስለነበረው የወልቃይት ጠገዴ የአማራ ብሔርተኝነት የማንነት ጥያቄ ስብሰባ የታዘብኩት ማስቀመጥ እሻለሁ፡፡ ሐሙስ እለት ላንድ ማርክ ሆቴል ስደርስ የእቴጌ ምንትዋብ የስብሰባ አዳራሽ ሞልቶ መፈናፈኛ አልነበረውም፡፡ ውስጥ ገብቼ አንዳንድ ነገሮችን ሪከርድ ለማድረግ ብሞክርም መሹለኪያ መንገድ ጠፋ፡፡ ስለዚህ የነበረኝ አማራጭ ውጭ ላይ ሆኖ በሞንታርቦው የሚነገረውን ማዳመጥ ነበር፡፡ ስብሰባውን የአዘጋጁት የጎንደርና የዳባት አገር ሽማግሌዎች ናቸው፡፡ ወልቃይት ቀድም ባሉት ጊዜያት የቆላ ወገራ አካል ሆኖ አውራጃው ዳባት ነበር፡፡ በዚህም ይመስላል የዳባት የአገር ሽማግሌዎች ከጎንደር ከተማ ጋር በመቀናጀት ስብሰባውን የአዘጋጁት፡፡ ኮሚቴዎቹ የደረሱበትና እየገጠማቸው ያለውን ነገር ሲያስረዱ ሕዝቡ ላይ የቁጭት፣ የንዴትና የተስፋ ስሜቶች ተደባልቀው ይነበቡ ነበር፡፡ በዚሁ ሰሞን በወልቃይት፣ በጠገዴና በኹመራ አካባቢዎች ለሠፈራ ከመጡት የትግራይ ተወላጆች በተጨማሪ በመኪና እየተጫኑ እየመጡ ‹‹ያልተመለሰ የማንነት ጥያቄ የለንም፤ ጸረ ሰላም ኃይሎችን አንታገስም…›› ወዘተ የሚሉ የማወናበጃና የማስፈራሪያ መፈክሮች በሰፊው የመንግሥት መገናኛ ብዙሃን ሽፋን ሰጥተዋቸው ሲስተናገዱ ሰንብተው ነበር፡፡ ነገር ግን የአማራ ተወላጆች ነን ላሉት እንኳንስ ሰላማዊ ሰልፍ ሊፈቀድ ቀርቶ የቤት ውስጥ ስብሰባም ተከልክለዋል፤ አማርኛ ሙዚቃ እንዳያደምጡ ተደርገዋል፡፡ አልፎም ወደ አገራቸው ለመሔድ ኬላዎችን ተሸለክልከው ነው፡፡

የማንነት ጥያቄ አስተባባሪ ከሆኑት መካከል ኮሎኔል ደመቀ የሚባሉት ይህን አስመልክተው ሲናገሩ ‹‹የእነርሱን ትግሬነት እኛ አልካድንም፤ እኛ የምንለው የእኛም አማራነት ይታወቅ ነው፡፡ አማራ የሆነ ሰው እንዴት በግዴታ ትግሬ ሊሆን ይችላል? በግዴታ እንዴት ማንነት ሊሰጠን ይችላል? እኛ እኮ በትግርኛ መርዶ ሰምተን በአማርኛ የምናለቅስ ነን፤ በትግርኛ የሰርግ ጥሪ ተላልፎልን በአማርኛ የምንዘፍን ሕዝብ ነን፡፡ ሕወሓት ጭቆና ወደ ጫካ አስወጣኝ ብሎ እኛ ላይ ያልፈጸመው በደል የለም፡፡ አማራ ነን ብሎ መናገር ምንድን ነው ጸረ ሰላም የሚያስብለው? ጠመንጃ መያዝ ለወልቃይት ሕዝብ ተራ በጣም ተራ ነገር ነው፡፡ ሆኖም ይህ የሚጠቅም ነገር ስላልሆነ በሕገ መንግሥቱና በሰላማዊ መንገድ ብቻ ጥያቄያችን እየቀርብን ነው፡፡ ይህ ጥያቄ የወልቃይት ብቻ ሳይሆን የመላው አማራ ነው፡፡ በእኛ ላይ የሚደርሰውን ግፍ ለማውገዝ የግድ አማራ መሆን አይጠበቅም፡፡ ትግሬዎች ራሳቸው ሕወሓትን በቃህ ሊሉት ይገባል›› በማለት በሰፊው አብራሩ፡፡ አቶ አታላይ ዛፌ የተባሉም በወልቃይት ሕዝብ በተለይ ደግሞ በሱዳን ወታደሮች እየተወሰዱ ስላለቁት የአማራ ወጣቶች፣ በሕወሓት ባለሥልጣናት ስለተደፈሩት ሴቶችና ተማሪዎች፣ ግሕንብ የምድር እስር ቤት ውስጥ ስላለቁት ወልቃይቴዎች በሰፊው ሲዘረዝሩ አንዳንዶች ያለቅሳሉ፤ ሌሎች ደግሞ ያጨበጭቡ ነበር፡፡ ፍጹም ድብልቅልቅ ያለ ስሜት፤ በቃ ደስታና ሀዘን፣ ተስፋና ተስፋ መቁረጥ፣ የዋህነትና በቀል፣ የአንድነትና የልዩነት…. ስሜቶች በአንድ ሰው ገላ ላይ ሳይታዩ አልቀረም፡፡

አንድ ስሙን ሳልሰመው ያለፈኝ የወልቃይት ተወላጅ ሁለቱን ወንድሞቹን የሕወሓት የጸጥታ ቡድኖች ወስደው እንዴት አሰቃይተው እንደገደሉበት ምስክርነቱን ሊሰጥ ማይክራፎኑን (የድምጽ ማጉያውን) ተቀበለ፡፡ ግን አልቻለም፡፡ ምንም እንኳ ግፉ የተፈጸመው ከዐሥር ዓመታት በፊት ቢሆንም አሁንም ድረስ በሐዘኑ ልቦናው እንደተሰበረ ነው፡፡ ሊናገር ሲል ትናገው መከፈት አልቻለም፡፡ በዐይኑ እንባ ፈሰሰ፡፡ ድምጹ ተቆራረጠ፡፡ ብዙ በጣም ብዙ በስብሰባው የነበሩ ሰዎች ዝም ብለው ማዳመጥ አልቻሉም፡፡ የሰዎች ኪስ ሲንኮሻኮሽ ይሰማል፡፡ ሶፍት ወይም ማኅረም ፍለጋ ነበር፡፡ የዛሬ ዐሥር ዓመት የተገደሉ ሰዎች ዛሬ መርዶአቸው የተረዳ መሠለኝ፡፡ ወንድ ልጅ ሲያለቅስ ማየት አልወድም፡፡ ቀረጻ ላይ ነበርኩ፡፡ እንባየ ተናነቀኝ፤ ታገልኩት፤ አልቻልኩም ፈሠሠ፡፡

ግለሰቡ ወንድሞቹን ከእናታቸው ነጥለው ወስደው አሰቃይተው ገድለውበታል፡፡ እርሱም አገር አለኝ ብሎ ተመልሶ አያውቅም፡፡ እንኳን ወልቃይት ሊሔድ ቀርቶ ጎንደር ኹመራ መውጫን ወለቃን አልፎ አያውቅም፡፡ በሐዘን የተሰበረ ልብ ይገርማል፡፡ በወልቃይት ሕዝብ ላይ ሕወሓት የፈጸመው ግፍ በቀላሉ ተነግሮ እንደማያልቅ ለመረዳት ችያለሁ፡፡ ሰዎች ተገድለው በአዲ ረመጥ ከተማ በመኪና ላይ ተጭነው ለሕዝብ መቀጣጫ እንዲሆኑ እንደ ደርግ የቀይ ሽብር ሰለባዎች በዚህ ዘመን የተፈጸመው ከወልቃይት ሕዝብ ውጭ የትም አይኖርም፡፡ አማራ በግዴታ ወደ ትግሬነት የተቀየረው ከወልቃይት ሕዝብ ውጭ በአገራችንም በዓለማችንም አይኖርም፡፡ እውነታው ይሔ ነው፡፡ ከሌሎች የአማራ ክልል አካባቢዎች እኛም ጋ መጥታችሁ ጉዳዩን አስረዱን የሚሉ ጥያቄዎች ብዙ ነበሩ፡፡

ጎንደር ስሔድ ምሽት ላይ ብዙ ጊዜ ወደ አጼ በካፋ የባህል ምሽት ማዝገሜን አልተውም፡፡ ጥሎብኝ የዚህ የባህል ምሽት እወደዋለሁ፡፡ የዛሬው አካሔዴ ግን ለመዝናናት እንዳልሆነ ብናገር ተአማኒነት ስለማይኖረው ብዙም ምክንያት ማቅረብ አልሻም፡፡ ብዙ ዜጎቻችን በርሃብ ጠኔ የሚበሉትን አጥተው እየተቸገሩ እንደሆነ አውቃለሁ፡፡ ይህንንም አይቻለሁ፡፡ በሰፊው ወደፊት ስለምሔድበት አሁን አልቀላቅልም፡፡ ቀን ላይ በወልቃይቶች ላይ የደረሰውን ስሰማ በእውነቱ እድሜ ልኬን በሐዘን የምኖርም መስሎኝ ነበር፡፡ ነገር ግን የሰው ልጅ ጠንካራ ፍጥረት ነውና የሐዘን ብዛት አጥንቱን አይሰብረውም፤ የመደሰቻ ሕዋሳቱን አያደነዝዝም እንጅ ትንሽ ብቻ በቂ ነበር፡፡ የሆነው ሆኖ አዝማሪ ምን አለ ለማለት ነበር የገባሁት፡፡

ተንኮለኛው ጋዜጠኛ ተስፋየ ገብረ አብ አንድ ጊዜ ጎንደር ሒጄ ሰማሁት ያላቸውን የአዝማሪ ግጥሞች አስታወስኩ፡፡

ጎንደር አገር ጠፍቶ ሲፈለግ ሌሊት

ቀን ታዲሱ ጋራ ሲሔድ አየሁት፤

በረከት አገሩ ስለናፈቀው

ዳሸን አናት ሆኖ አስመራን አየሁ፡፡

እነዚህን ግጥሞች ጎንደር በሔድኩ ቁጥር አዝማሪ ለአዝማሪ ቤት እየዞርኩ ልሰማቸው ፈልጌ አልተሳካልኝም፡፡ ግን የጎንደር አዝማሪ ከእነዚህ በላይ የግጥም ቅኔዎች ማሽሞንሞን ይችላል፡፡ ለምሳሌ ይህን ግጥም በሕሊናችሁ በማሲንቆ አጃቢነትና በመረዋ የቡርቧክስ አዝማሪ ድምጽ ስሙት (ቡርቧክስ ከጎንደር ከተማ 40 ኪሎ ሜትር ያክል የሚርቅ ማክሰኝት የምትሰኝ ከተማ ወደ በለሳ መውጫ በኩል ያለ የገጠር ቀበሌ ሲሆን የበርካታ አዝማሪዎች ቀዬ ነው)፡፡

ኧረ አገሬ ጎንደር ሸንበቆው ማማሩ፣

አገሬ ወስከንቢት ሸንበቆው ማማሩ፤

ኧረ አገሬ ቋራ፣ መተማ አርማጭሆ ሸንበቆው ማማሩ

አገሬ ወልቃይት፣ ቃፍታና ኹመራ ሸንበቆው ማማሩ፣

ቆርጠው ቆርጠው ጣሉት ለም-አገር እያሉ!

አዝማሪው አገሩን በሸንበቆ መስሎ ለም ለም የሆነው ሁሉ ተቆርጦ አንድም ለሱዳን አሊያም ለታላቋ የትግራይ ሪፐብሊክ ምስረታ መወሰዱን በቁጭት ነው በቅኔ የሚገልጸው፡፡ የሆነው ሆኖ በዚያ ቀን አብዛኛው በበካፋ የባህል ቤት ሲዘፈን ያመሸው ስለወልቃይት ነው፡፡ አንድ ራሰ በራ ድምጸ መረዋ አዝማሪ አለ፡፡ የድምጹ ነገር ወፍ ከሰማይ ያወርዳል፤ ወይንም በአገራችን አባባል ነብር ይጠራል፡፡ የፋሲል ደመወዝን ‹‹አረሱት መተማ፣ አረሱት ኹመራን የውም የእኛን እጣ፣ እነርሱ ምን ያርጉ ከእኛ ሰው ሲታጣ›› ያለ ጊዜ የምድር ቤት ውስጥ ያለው አዳራሽ በጩኸት ተናወጠ፡፡ መቼም በጩኸት ከኢያሪኮ ከተማ ውጭ የፈረሰ ግንብ አልሰማሁም እንጅ ያን እለት የነበረው ጩኸት ከዚህ ላይ ለመግለጽ ቃላት መፈለግ ግድ ይለኛል፡፡

አዝማሪው ያዘምራል፡፡ እንዲህ በማለት

ኧረ አገሬ ጎንደር ሰሜን ጃናሞራ ወልቃይት ጠገዴ፣

ለራበው እንጀራ ለጠገበው ጓንዴ!

ወደ መድረክ ሰው ሁሉ መቶ ብር መወርወር ጀመረ፡፡ በዚያ ምሽት ቤቱን አይቶ የማያውቅ እንግዳ ሰው ቢገባ የቤቱ ሕግ መስሎት መቶ ብር እንደሚወረውር በእርግጠኛነት መናገር እችላለሁ፡፡ መድረክ አካበቢ ወደ አዝማሪው ስመለከት ውር ውር የሚሉ አረንጓዴ ቢራቢሮዎች ባለማሲንቆውን ሸፍነውታል፡፡ አዎ ቢራቢሮዎች አይደሉም፤ የባለ መቶ ብር ኖቶች እንጅ፡፡ ከዚህ ቤት ውስጥ የታመቀ ብሶት ፈንድቷል፡፡ የተጠራቀመ ቁጭት ፈሷል፡፡ ወጣቱ ደሙ ፈልቷል፡፡ ባርነትን በቃህ የሚል ይመስላል፡፡ ማንም ይህን የተናገረ የለም፤ እኔ ግን እያንዳንዱ ሰው ፊት ላይ ያለውን ስሜት አንብቤዋለሁ፡፡ ሊመርጅ የገባው የደህነንቱም ሰው ስሜት ቢሆንም!!

እስኪ አንድ ሰው እስክስታ እየመታ ሲያነባ፣ ግማሽ ፊቱ የብርሃን ጸዳል ወርሶት ግማሹ ግን የዳመነ ሲሆን፣ ውስጡን በነገር ሞልቶ መተንፈስ አልችል ሲል፣ ሁለት ፍጹም ተቃራኒ ስሜቶች በአካላቱ ላይ ሲነበቡበት ያያችሁት ሰው አለ? ወይስ ይህ ስሜት ገጥሟችሁ ያውቃል? እኔ በዚያ ቤት ውስጥና በዚያ ሰዓት ያየሁት ግን ይህ ነው፡፡ ቤቱን ሁለት ፍጹም ተቃራኒ መናፍስት ወርሰውት አምሽተዋል፡፡

የሚቀጥል

ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ

By Achamyeleh Tamiru

ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ

ወያኔ የጎንደርን መሬት ለሱዳን አሳልፎ በመስጠት አማራውን የማጥፋት ፕሮጀክቱን አጠናክሮ ቀጥሏል! ሆዳሙ አማራ ግን ይህንን እያጠፋው ያለውን የግፍ አገዛዝ 35ኛ ዓመት ውልደትና የአማራውን የእልቂት አመታት ድል ባለ ድግስ ሲያከብር «አይ አማራ፤ ያን ሁሉ አማራ የጨረሰን ስርዓት፣ ሊያጠፋው የታገለውንና መንግስት ከሆነም በኋላ እያጠፋው ያለውን ቡድን ልደት እንዲህ ድል አድርጎ ይደግስና ያክብር» እየተባለ ልክልኩን ሲነገረው ሰንብቷል። ይህም ሲያንሰው ነው! ሆዳም የሆነ የጉድ ህዝብ!

የጦጣ ግንባር የምታህል የትግራይ መሬት የሆነችውን ባድሜን «ኤርትራ ልትወስድብን ነው» ብሎ ወያኔ ጦርነት ውስጥ ገብቶ 80 ሺህ የሚሆኑ የድሀ ልጆችን ካስጨረሰ በኋላ አለማቀፍ የድንበር ኮሚሺን ተቋቁሞ ባድመን ለኤርትራ ቢወስንም ወያኔ ግን የትግራይ መሬት የሆነውን ባድመን ለኤርትራ ላለመስጠት አሻፈረኝ በማለት እስካሁን ተቀምጦ ጅቡቲን የሚያህል የአማራውን መሬት ግን በድብቅ ለሱዳን መስጠቱ የማይቆጨው ሆዳሙ የአማራ ህዝብ ከገዳዩ ኋላ ሲጎተት ይኖራል! ዓሰብም ወሎ ስለነበረች ነው ተላልፋ የተሰጠች። አሰብ ትግራይ ቢሆን ኖሮ ከባድመ በላይ ደም ይፈሳል እንጂ ተላልፋ አትሰጥም ነበር። የሰሜን ወሎ መሬት ወደ «ትግራይ ሪፑብሊክ» የተካተተው፤ መተከል ከጎጃም ተቆርሶ ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ የገባው፤ ወልቃይትና ሁመራ ከጎንደር ተቆርሶ ወደ «ትግራይ ሪፑብሊክ» የተጠቃለለው ሆዳሙ አማራ ሳያውቅ አይደለም። ይህንንና ሌላውን በአማራ ላይ የደረሰ በደል እየገጣጠመ ምስል የማይፈጥር ደንቆሮና ሆዳም ብቻ ነው።

እኔ ካሁን በኋላ ወያኔን ማውገዝ ልተው ነው። ወያኔ ዛሬ እያደረገው ካለው ውስጥ አንድም ያልታገለለት ነገር የለም። የታገለለትን ለምን አሳካህ ብሎ መውቀሱ ተገቢ አይደለም። ወያኔ ጫካ ሀ ብሎ ሲገባ ለሚመሰርተው የትግራይ ሪፑብሊክ መንግስት ጠላቱ አማራ እንደሆነና አማራ ካልጠፋ የትግራይ ሪፑብሊክ መንግስት እውን እንደማይሆን በጥቁርና ነጭ ብራና ፍቆ ቀለም በጥብጦ ማኒፌስቶ በመጻፍ ነው የበረሀ ትግሉን የጀመረው። በአስራ ሰባት አመታት የትግል ቆይታውም የትግራይን ወጣት የቀሰቀሰው፤ ቄስ መነኩሴውን ከጎኑ ያሰለፈው «አማራ ሰይጣን ነው፤ ሰይጣን ስለሆነ ይህን ሰይጣን ተረባርበን ማጥፋት አለብን» ብሎ ያነሳሳው ሰይጣኑን አማራ ለማጥፋት ነው። ታዲያ ዛሬ ወያኔ ያንን የታገለለትን አማራውን የማጥፋት ግቡን እየደረሰበት ቢመጣ ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው? ስንት ሺ የትግራይ ወጣቶችን መስዕዋት ያደረገበት የትግል ውጤቱ አይደለም እንዴ?

ከፍብዬ እንዳልሁት ለአማራው መጥፋት ተጠያቂው ራሱ ሆዳሙ አማራ ብቻ ነው። ከጅምሩ ጀምሮ ወያኔዎች ሲታገሉ [የአማርኛ ትርጉሙ የግርጌ ማስታወሻው ላይ ይገኛል]፤

*« አማራ አድጊ፣ አማራ አሻ፣ አማራ ጉሀፍ » እያሉ እየፎከሩበት»፤

*«ገረብ ገረብ ትግራይ፣
መቃብር አምሃራይ!» በማለት ታጋዮቻቸውን ያጀገኑበት፤

*«ጎበዝ ተኻወት ተጋዳላይ ትግራይ፤
አርኪብካ በሎ ንዚ-ሃሻ አምሃራይ!
ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» በማለት እየተቀኙበት ሊያጠፉት ታፍለው ሳለ የጎንደርና የጎጃም፤ የወሎና የሸዋ ህዝብ ግን መንገድ እያሳዬ፣ «የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው» ብሎ አብሯቸው እየተዋደቀ፤ ቋንጣና ቆሎ እያዘጋጀ አዲስ አበባ ሚንልክ ቤተ መንግስት ድረስ አጅቦ የሚጠፋበትን በትረ ስልጣን ያስረከበው ራሱ ሆዳሙ አማራ ነው።

ወያኔዎች ስልጣን ከያዙ በኋላም «ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ» እያለ ሊታደጉት የተነሱትን ፕሮፌሰር አስራትንና መሰል የህዝብ ልጆችን ቁጭ ብሎ እያየ በወያኔ ያስገደለው እሱ ራሱ አማራው ነው። ከዚያም አልፎ አማሮች እንደ አውሬ ባገራቸው እየታደኑ ሲገደሉ «ወያኔ ከሰራው የአማራ ክልል ውጭ ያሉ አማሮችን አላውቅም» ሲል የወያኔው ሹመኛ፣ ሆዳሙ አማራ ግን በተለመደው የሰነፍ ፍልስፍናው አይቶ እንዳላዬ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ የሆነው ራሱ ሆዳሙ አማራ ነው።

ይህ ሆዳም ዝህብ ሊታደጉት ካብራኩ የወጡ ልጆቹን ሁሉ አሳልፎ ለወያኔ በመስጠት አስበልቶ ሲያበቃ የት እንደወደቁ እንኳ ሳይጠይቅ ገዳዩ የመለስ ዜናዊ ሲሞት ግን፣ ኩታውን አዘቅዝቆ፣ ፊቱን ፈጅቶ፣ ደረቱን እየደቃ ከእለት እስካርባ ሀዘን ተቀምጦ የጨካኙን ተስካር ድል አድርጎ ደገሰ። ዛሬ የሚጮህለት ያጣውም ጠላቶቹን አልቅሶ ሲቀብር ለተቆርቋሪዎቹ አንድ ዘለላ እንባ እንኳ በመንፈጉ ነው። ስለዚህ አማራው እያለቀ ያለው ሆዳሙ አማራ በሰራው ስህተቱ ነው። በዚህም የተነሳ ዛሬ ለራሱም ለኢትዮጵያም ሸክምና Helpless Creature ሆኗል። በየእስር ቤቱ አማሮችን ሱሪያቸውን እያስፈቱ «አማራው ሱሪውን መፍታቱን እንድታውቅ ነው» እያሉ ሲሳለቁባቸው፤ ዘሩን እንዳይተካ የአማራ ወንድ በየማጎሪያው ሲኮላሽ፤ እናቶች የሚያመክን መርፌ ሲወጉ ሆዳሙ አማራ ግን ምንም እንዳልደረሰበት አይቶ እንዳላየ የዝምታ ግርማ ውስጥ ተዘፍቆ ይኖራል።

አውቃለሁ ይህንን በመናገሬ «አድጊ፣ አሻ፣ ጓሀፍ» እያሉ በፎከሩበት፤ «ገረብ ገረብ ትግራይ መቃብር አምሃራይ» በማለት ታጋዮቻቸውን ያጀገኑትን፤ «ጎበዝ ተዓወት ተጋዳላይ ትግራይ፣ አርኪብካ በሎ ንዚ ዓሻ አምሃራይ፤ ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» በማለት ያጠፉትን ወያኔችን አንድም ያልተነፈሰ ሆዳም አማራ ሁሉ በእኔ ላይ እንደሚነሳ ይገባኛል። የአማራው ጠላት ሆዳሙ አማራ እንደሆነ ስለማቅ ግን ማንም ሆዳም እየተነሳ በበላበት ቢጮህ አይገደኝም።

ሰው የሌለው የጎንደር መሬት ግን እንዲህ እያለ ይጮሃል…..

መተማ ሁመራ ቋራም ሆድ ሲብሰው፣
ሱዳን ተሰደደ መሬቱም እንደሰው፤

የፕሮፌሰር አስራት ልጅ የሆነው የጎንደር ገበሬም ብቻውን ያለሰው ያለዘር ቢጮህ ምን ያደርጋል ብሎ እንዲህ ይላል….

በሮቼን አምጡልኝ አርጀ ልብላቸው፣
ደግሞ እንደመሬቱ ሳይቆረጥማቸው፤
መሬቱን ሲያርሱብኝ እያየሁ ዝምብዬ፣
ዘር ሳይዙ ማረስ ምን ያደርጋል ብዬ፤
እንዲህ ያለ ዘመን የተገላቢጦሽ፣
አህያ ወደ ቤት ውሻ ወደ ግጦሽ።
===================================================

የግርጌ ማስታወሻ
*«ገረብ ገረብ ትግራይ፣
መቃብር አምሃራይ!»
ትርጉም በግርድፉ:- የትግራይ ተራሮች የአማራ መቃብር ይሆናሉ

*«ጎበዝ ተኻወት ተጋዳላይ ትግራይ፤
አርኪብካ በሎ ንዚ-ሃሻ አምሃራይ!
ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» እያሉ

ትርጉም:- ጎበዝ ድል አድርግ የትግራይ ተጋዳላይ፤ ተከትለህ በለው ይህን ጅል አማራይ

* « አማራ አድጊ፣ አማራ አሻ፣ አማራ ጉሀፍ »
ትርጉም :- አማራ አህያ፣ አማራ ጅል፣ አማራ ቆሻሻ
===================================================

ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ እነሆ! ይህን ዝግጅት የግድ መደመጥ ያለበት ነው። ኢሳት ምስጋና ይገባዋል! ወንድማገኝ ተባረክ!

http://ethsat.com/…/esat-tikuret-wondimagegne-discussed-wi…/

የትግሬ-ወያኔ አቅጣጫ ከ፪ሺህ፯ ዓ.ም. በኋላ የሞረሽ-ወገኔ መግለጫ

Moresh

የትግሬ-ወያኔ አመራር በቅርቡ ባደረገው ስብሰባ ዐማራን ፈጽሞ ሳያጠፋ እንቅልፍ እንደማይወስደው ዳግም አረጋገጠ!

image

«ትናንት፣ ዛሬም ሆነ ነገ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ዐማራው ስለሆነ፣» እያንዳንዱ ትግሬ ዐማራን በማጥፋት እንቅስቃሴ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን፣ የወያኔ የአገር-ውስጥ እና የውጭ የስለላ ቡድኖች ከፍተኛ አመራሮች በጥናቶቻቸው እንዳሣዩ የታመኑ የሞረሽ-ወገኔ ምንጮቻችን አረጋገጡ። የመረጃ ምንጮቻችን እንደሚያስረዱት፣ አጥኚዎቹ ከሕወሓት ፖሊት ቢሮ በተሰጣቸው መመሪያ መሠረት የትግሬ-ወያኔን ዘረኛ አገዛዝ ያለፉትን የ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት ጉዞ መዝነው፣ ለሥልጣኑ አስጊው ማን እንደሆነ በመተንተን፣ ከ፪ሺህ፯ ዓ.ም. በኋላ የትግሬ-ወያኔ እንዴት መቀጠል እንዳለበት ዝርዝር ጥናት አቅርበዋል።
በትግሬ-ወያኔ የስለላ ተቋሞች ከፍተኛ አካሎች አማካይነት የተደረገው ይህ ዝርዝር ጥናት፣ «የመፍትሔ ኃሣብ ነው» ያለውን ለሕወሓት ፖሊት ቢሮ ማቅረቡን ምንጮቻችን ገልጸዋል። በስለላ ቡድኖቹ አንኳር የጥናት ውጤት መሠረት ወያኔ ገና «ሀ» ብሎ የትጥቅ ትግል ሲጀምር ከኢምፔሪያዝም በላይ እና በፊት «ዐማራ የትግራይ ሕዝብ ጠላት ነው» ብሎ መፈረጁ ትክክል እንዳልነበር፣ የትግሬ-ወያኔ ሥልጣን ከያዘ በኋላም ቀደም ሲል የፈጸመውን ስሕተት በማረም እና በማስተካከል ፋንታ በያዘው የቆየ የተሳሳተ ፍረጃ ገፍቶ በዐማራው ላይ ያደረሰው ጥፋት፣ እኒህ ሁሉ ተደማምረው ዐማራው «ትግሬ ጠላቴ ነው» ብሎ እንዲያስብ እና በነገዱ ዙሪያ እንዲሰባሰብ እንዳስገደደ ያመለክታል። ይህም ለተተኪው የትግራይ ትውልድ ቋሚ ጠላት የገዛ መሆኑ ተጠቅሷል። ከዚህ በተጨማሪም፣ ከሻዕቢያ ጋር የተገባው መቋጫ ያልተገኘለት ጦርነት የትግራይን ሕዝብ ከሥጋ ዘመዱ ከኤርትራ ሕዝብ ጋር ደም ያቃባ እና ቋሚ የደም ጠላት የገዛለት መሆኑ ተመልክቷል። በመሆኑም የትግራይ ሕዝብ ከላይ በኤርትራውያን፣ ከታች እና ከመሐል ደግሞ በዐማራው መካከል ሣንዲዊች ተደርጎ እንዲያዝ ያደረገ በመሆኑ፣ የወያኔ የ፳፬(ሃያ አራት) ዓመታት የሥልጣን ጉዞ ለመጭው የትግራይ ትውልድ ደም የገዛለት፣ የሥጋት ምንጮችን ያራባበት እንደሆነ የስለላ ቡድኖቹ የጥናት ውጤት አረጋግጧል።
የስለላ ቡድኖቹ ጥናት ለወደፊት የትግሬ-ወያኔ እንዴት በሥልጣን ላይ መቀጠል እንደሚችል የሚከተለውን ምክር መስጠቱ ታውቋል። ለጊዜው ወያኔ በሥልጣን ላይ በመሆኑ፣ ችግሩን ማስተዋል ቢሣነውም፣ የትግራይ ትውልድ በመጭዎቹ ዘመናት የሚታወቀው በሀገር ከሃዲነት፣ በኢትዮጵያ አፍራሽነት፣ ኢትዮጵያውያንን በጎሣ አቧድኖ በማጫረስ እና አገሪቱን ዝግ መሬት በማድረጉ እንደሚሆን ጥናቱ ያወሣል። ለወደፊቱም ወያኔ እንዴት መቀጠል እንዳለበት የሰጠው የመፍትሔ ኃሣብ፥ የተፈጸመውን ጥፋት በምንም መልኩ ወደኋላ ተመልሶ ማስተካከል ስለማይቻል፣ ማድረግ ያለበት በዝምታ ወደፊት መቀጠል መሆኑን፣ በአገሪቱ ውስጥ ካሉት ነገዶች ትግሬን የሚያሰጋው ሌላ ማንም ሳይሆን፣ ዐማራው መሆኑን፣ እና ይህ ነገድ በምንም ተዓምር የመደራጀት ዕድል እንዳያገኝ ወያኔ የሚቻለውን ሁሉ ማድረግ እንዳለበት ያስገነዝባል። ለዚህም ግብ ተግባራዊነት የተነደፉ ስልቶች፦
ሀ) ዐማራዎች ከሁለት በላይ ሆነው እንዳይንቀሳቀሱ የተጠናከረ የስለላ እና የክትትል መረብ እንዲዘረጋ ማድረግ፤
ለ) ወደውጪ አገር ለመሰደድ የሚፈልገውን ዐማራ በተለያዩ ስልቶች እንዲሰደድ ሁኔታዎችን በስውር በማመቻቸት ማሰደድ፤
ሐ) በአገር ቤት ያለውን እና ለመሰደድ ፈቃደኛ ያልሆነውን ደግሞ አንገቱን ሳያቀና በልዩ ልዩ መንገዶች ማስወገድ፤
መ) አንገታቸውን ያቀኑትን በተቀነባበረ መንገድ በሐሰት በመክሰስ በፍርድ ቤት የረጅም ጊዜ እስር በማስፈረድ ዕድሜያቸውን በእስር እንዲጨርሱ እና ተከታዮቻቸው ሞራላቸው እንዲላሽቅ ማድረግ፤
ሠ) ድኃ ከዕለት ምግቡ በቀር ሌላ ነገር ማሰብ ስለማይችል፣ ዐማራውን በድኅነት ማጥ ውስጥ የሚከቱ ስልቶችን በመንደፍ ከሆዱ አልፎ ሌላ ነገር አንጋጦ እንዳያይ ማድረግ፤
ረ) ዐማራው በብዛት ተከማችቶ የሚገኝባቸውን ከተሞች እና መንደሮች በልዩ ልዩ የግንባታ ስበቦች በማፍረስ የዐማራውን የአብሮነት እና ማኅበራዊ ትሥሥር መበጣጠስ፤
ሰ) ሌሎች ነገዶች፣ በተለይ ኦሮሞዎቹ፣ ከዐማራው ጋር ምንም ዓይነት ቀና ግንኙነት እንዳይኖራቸው በሁለቱ ነገዶች መካከል ልዩነቶችን የሚያሰፉ የፕሮፓጋንዳ ሥልቶችን ቀይሶ መንቀሳቀስ፣ የሚሉ ይገኙበታል።
ለእነዚህም ስልቶች ተግባራዊነት፦
ሀ) እያንዳንዱ ትግሬ በስለላ ንቁ ተሳታፊ እንዲሆን ማድረግ፣
ለ) የትግራይ ሕዝብ የትግሉ መሠረት እንደመሆኑ መጠን ከአሁኑ በተሻለ መንገድ የሁሉም ነገሮች ተጠቃሚ በማድረግ በሙሉ ኃይሉ ከሕወሓት ጎን እንዲሰለፍ ማድረግ፤
ሐ) ሕወሓት በሥልጣን ላይ ከሌለ የትግሬ ነገድ ዛሬ የጨበጠው የፖለቲካ እና የኢኮኖሚ የበላይነት የማይቀጥል ከመሆኑም በላይ በወያኔ ተባባሪነት ተጠያቂ የሚሆነው ሕዝብ ጥቂት እንደማይሆን አውቆ ለሕወሓት ኅልውና የተለመደውን ትብብር ማድረግ እንዳለበት ያላሰለሰ ትምህርትና ቅስቀሳ መስጠት የማይታለፉ ተግባሮች መሆናቸውን የጥናት ቡድኑ መክሯል።
በቅርብ ሣምንታት ይህ አዲሱ የትግሬ-ወያኔ ዕቅድ በተግባር መተርጎም መጀመሩን የሚያመለክቱ ድርጊቶች ተበራክተዋል። ለአብነት ያህል ከሦሥት ቀናት በፊት ሰኔ ፰ ቀን ፪ሺህ፯ ዓ.ም. ሣሙኤል አወቀ የተባለውን እና ሰማያዊ ፓርቲን ወክሎ በምሥራቅ ጎጃም ዞን ለፓርላማ አባልነት የተወዳደረውን የ፳፱ (ሃያ ዘጠኝ) ዓመት ወጣት በአሠቃቂ ሁኔታ ደብረማርቆስ ከተማ ውስጥ የገደሉት አንድ ምሣሌ ነው። ቀደም ብሎም በሚያዝያ እና በግንቦት ወራት አያሌ የዐማራ ተወላጆች ለግድያ፣ ለእሥር እና ለእንግልት መዳረጋቸው የአደባባይ ሚሥጢር ነው።
የትግሬ-ወያኔዎች እንዲህ ያስባሉ፣ ኃሣባቸውንም በተግባር ይተረጉማሉ። ዐማራውስ ራሱን ከፈፅሞ ጥፋት ለማዳን ምን ያስባል? መጥፋት ወይስ መክቶ ጥፋትን መከላከል? እንደሞረሽ ወገኔ አቋም «ጅብ ከሚበላህ፣ በልተኸው ተቀደስ» ነውና፤ ይህ አገርን እና ትውልድን አጥፊ የትግሬ-ወያኔ ናዚያዊ ቡድን አጥፍቶን ከመጥፋቱ በፊት እንቅስቃሴውን የሚያመክን የተግባር እርምጃ ይጠይቃል። ለዚህም ዐማራው ተደራጅቶ ራሱን እና አገሩን ከፈጽሞ ጥፋት ሊታደግ ይገባል ብለን እናምናለን። ይህ ጉዳይ «ቆይ እንመካከር፣ እንወያይ» የሚባልበት አይደለም። አፋጣኝ የተግባር እርምጃ ይጠይቃል።

ዐማራን ከፈጽሞ ጥፋት እንታደግ!
ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት
mwaoipr@gmail.com

Taitu Hotel, EPRDF and Arson

image

ADDIS ABABA – A few days before fire burned down Ethiopia’s historic Taitu Hotel, a young woman reads out a satire in the company of a live jazz band:

A drop is just water but pierces the rock,
Let’s make noise till the nation wakes up,
Was my advice to you before I now know
That my whole idea is futile and hollow.

When film director and actor Meron Getnet read her satirical poem, it was like a lasting tribute to a country that has time and again failed to shrug off tyranny and rise up to honor.
Gone is Taitu Hotel along with the Jazzamba, where the gifted instrumentalists that kept Meron company used to play.
Taitu Hotel, EPRDF and ARSON
When on Monday the landmark hotel was going up in smoke, fire fighters began work after one hour, when the hotel was largely destroyed.
Witnesses said distance couldn’t be a reason as the fire station was only a five-minute drive away. The fire fighters were haggling how much they should be paid before the raging fire was brought under control and the hotel saved.
But ‘haggling’ was a cover-up. Well-informed sources say it is in the interest of the ruling party to keep destroying historical landmarks like Taitu’s, whose founder was the wife of Emperor Menelik II, a leader Ethiopians credit as the first modernizer of the country. Menelik is also hailed for leading a huge Ethiopian force that crushed Italian colonial invaders at the 1896 Battle of Adwa.
And such credits are what upset the ruling party, which has lived demonizing Emperor Menelik as a divider and conqueror of “nations and nationalities.”
“Taitu Hotel is destroyed as the work of an arsonist, and there is no better arsonist than EPRDF,” one source with close ties to the ruling party told Ethiomedia by phone. How many private businesses have been burned down because the ruling party wants to dominate the market, asked the source.
“If they can’t send you to prion,” he quipped, “they burn you down.”
Without the need for evidence, the foreign media may report Ethiopia as one of the fastest economies in Africa. For the citizens of the country, however, they believe their country is one of the failed states in Africa reeling under a regime that is not only a tyrant but also a merciless arsonist.

Source: Ethiomedia editor@ethiomedia.com

TPLF shockingly admits failures in Ethiopia

By Admasu Belay

Lessons for those who harp on TPLF’s non-existing “Economic Growth” and other “achievements”

image

“The document, seen by the Financial Times, is a sobering reminder of the risk of investing in one of Africa’s less developed nations. With gross domestic product per capita at less than $550 per year, Ethiopia is the poorest country yet to issue global bonds.

In the 108-page prospectus, issued ahead of its expected $1bn bond, Ethiopia tells investors they need to consider the potential resumption of the Eritrea-Ethiopia war, which ended in 2000, although it “does not anticipate future conflict”.

There is also the risk of famine, the “high level of poverty” and strained public finances, as well as the possible, if unlikely, blocking of the country’s only access to the sea through neighbouring Djibouti should relations between the two countries sour.

Addis Ababa, Ethiopia’s capital, also warns that it is ranked close to the bottom of the UN Human Development Index – 173rd out of 187 nations – and cautions about the possibility of political turmoil. “The next general election is due to take place in May 2015 and while the government expects these elections to be peaceful, there is a risk that political tension and unrest?.?.?.?may occur.” ”

Since it came to power over 20 years ago, the TPLF regime has always declared its achievements in Ethiopia’s political and economic sectors. Everybody knows the state media ETV and its daily nonstop propaganda of how much better Ethiopia has become over the years. Not only that, TPLF has been telling the international community about how it changed and transformed Ethiopia. So much so that it had even deceived some Bush and Obama adminstration officials to believe its lies.
But after over 20 years, the London-based Financial Times (FT) reported today that TPLF has finally admitted its massive failures in Ethiopia.
Shockingly, the TPLF admitted its disasterous policy of landlocking Ethiopia and its economic impact as well as the risk of another famine in Ethiopia.
For the last two decades, this “F word,” was banned by Meles and all his TPLF disciples. In the past, If any foreign officials dared to use the words “famine” and “Ethiopia” in the same sentence, the wrath of TPLF’s “ministry of foreign affairs (mfa)” would attack and humiliate them with endless MFA press releases. Meles himself told Ethiopians to forget about famine and promised that even our poorer people “will eat three times a day very soon.” That promise was made in 1994! Ironically today, the TPLF government sent a document to international investors, admitting another ” risk of famine, the high level of poverty” in Ethiopia, according to the Financial Times.
Not only has Ethiopia lost most of its hard currency reserves but the “steadily depreciating exchange rate may adversely affect Ethiopia’s economy?,” according to the TPLF document.

That is not all. TPLF also admitted the chance of “resumption” of the war with Eritrea and more unrest from “political turmoil” as well as bad relations with Djibouti causing the “blocking of the country’s only access to the sea.”

It is about time TPLF accepted its failures!

Out of TPLF’s top five policy changes since it removed Mengistu regime in 1991, it has now admitted four policies have failed already.

On Eritrea policy and access to the sea. (ADMITTED FAILURE)
Avoiding drought and famine (ADMITTED FAILURE)
On Improving Ethiopian economy/fiscal policies (ADMITTED FAILURE)
Political reform and democratization (ADMITTED FAILURE)
Ethnic federalism (No admission yet)
Regarding the 5th TPLF policy, everybody knows TPLF has failed. Soon it will admit this failure too.
In 1995, TPLF claimed its “ethnic federalism” system will empower tribes without dividing Ethiopians. But today, Ethiopia is the most ethnically divided country in the world. Ethnic hatred, propaganda and tensions today are the highest ever in history. Just like the 1990s Rwanda, tribalism has destroyed Ethiopian nationalism and humanity. Sooner or later, TPLF will be forced to admit its last and final failure.
Regardless, Today will go down in history as the day TPLF admitted that it has achieved almost nothing (other that a few tall buildings) since it removed the DERG regime in 1991. It has failed Ethiopia in every way possible. The only reason TPLF is still in power is because Ethiopians are peaceful people, unlike the warmongering and hate-filled TPLF.
For all those EPRDF ruling party supporters and TPLF footsoldiers worldwide, this must be the most embarasssing day. One single TPLF document has virtually dismissed over 20 years of ETV propaganda.

Copyright 2013 Ethiomedia.com. Email: editor@ethiomedia.com