ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ

By Achamyeleh Tamiru

ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ

ወያኔ የጎንደርን መሬት ለሱዳን አሳልፎ በመስጠት አማራውን የማጥፋት ፕሮጀክቱን አጠናክሮ ቀጥሏል! ሆዳሙ አማራ ግን ይህንን እያጠፋው ያለውን የግፍ አገዛዝ 35ኛ ዓመት ውልደትና የአማራውን የእልቂት አመታት ድል ባለ ድግስ ሲያከብር «አይ አማራ፤ ያን ሁሉ አማራ የጨረሰን ስርዓት፣ ሊያጠፋው የታገለውንና መንግስት ከሆነም በኋላ እያጠፋው ያለውን ቡድን ልደት እንዲህ ድል አድርጎ ይደግስና ያክብር» እየተባለ ልክልኩን ሲነገረው ሰንብቷል። ይህም ሲያንሰው ነው! ሆዳም የሆነ የጉድ ህዝብ!

የጦጣ ግንባር የምታህል የትግራይ መሬት የሆነችውን ባድሜን «ኤርትራ ልትወስድብን ነው» ብሎ ወያኔ ጦርነት ውስጥ ገብቶ 80 ሺህ የሚሆኑ የድሀ ልጆችን ካስጨረሰ በኋላ አለማቀፍ የድንበር ኮሚሺን ተቋቁሞ ባድመን ለኤርትራ ቢወስንም ወያኔ ግን የትግራይ መሬት የሆነውን ባድመን ለኤርትራ ላለመስጠት አሻፈረኝ በማለት እስካሁን ተቀምጦ ጅቡቲን የሚያህል የአማራውን መሬት ግን በድብቅ ለሱዳን መስጠቱ የማይቆጨው ሆዳሙ የአማራ ህዝብ ከገዳዩ ኋላ ሲጎተት ይኖራል! ዓሰብም ወሎ ስለነበረች ነው ተላልፋ የተሰጠች። አሰብ ትግራይ ቢሆን ኖሮ ከባድመ በላይ ደም ይፈሳል እንጂ ተላልፋ አትሰጥም ነበር። የሰሜን ወሎ መሬት ወደ «ትግራይ ሪፑብሊክ» የተካተተው፤ መተከል ከጎጃም ተቆርሶ ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ የገባው፤ ወልቃይትና ሁመራ ከጎንደር ተቆርሶ ወደ «ትግራይ ሪፑብሊክ» የተጠቃለለው ሆዳሙ አማራ ሳያውቅ አይደለም። ይህንንና ሌላውን በአማራ ላይ የደረሰ በደል እየገጣጠመ ምስል የማይፈጥር ደንቆሮና ሆዳም ብቻ ነው።

እኔ ካሁን በኋላ ወያኔን ማውገዝ ልተው ነው። ወያኔ ዛሬ እያደረገው ካለው ውስጥ አንድም ያልታገለለት ነገር የለም። የታገለለትን ለምን አሳካህ ብሎ መውቀሱ ተገቢ አይደለም። ወያኔ ጫካ ሀ ብሎ ሲገባ ለሚመሰርተው የትግራይ ሪፑብሊክ መንግስት ጠላቱ አማራ እንደሆነና አማራ ካልጠፋ የትግራይ ሪፑብሊክ መንግስት እውን እንደማይሆን በጥቁርና ነጭ ብራና ፍቆ ቀለም በጥብጦ ማኒፌስቶ በመጻፍ ነው የበረሀ ትግሉን የጀመረው። በአስራ ሰባት አመታት የትግል ቆይታውም የትግራይን ወጣት የቀሰቀሰው፤ ቄስ መነኩሴውን ከጎኑ ያሰለፈው «አማራ ሰይጣን ነው፤ ሰይጣን ስለሆነ ይህን ሰይጣን ተረባርበን ማጥፋት አለብን» ብሎ ያነሳሳው ሰይጣኑን አማራ ለማጥፋት ነው። ታዲያ ዛሬ ወያኔ ያንን የታገለለትን አማራውን የማጥፋት ግቡን እየደረሰበት ቢመጣ ጥፋቱ ምኑ ላይ ነው? ስንት ሺ የትግራይ ወጣቶችን መስዕዋት ያደረገበት የትግል ውጤቱ አይደለም እንዴ?

ከፍብዬ እንዳልሁት ለአማራው መጥፋት ተጠያቂው ራሱ ሆዳሙ አማራ ብቻ ነው። ከጅምሩ ጀምሮ ወያኔዎች ሲታገሉ [የአማርኛ ትርጉሙ የግርጌ ማስታወሻው ላይ ይገኛል]፤

*« አማራ አድጊ፣ አማራ አሻ፣ አማራ ጉሀፍ » እያሉ እየፎከሩበት»፤

*«ገረብ ገረብ ትግራይ፣
መቃብር አምሃራይ!» በማለት ታጋዮቻቸውን ያጀገኑበት፤

*«ጎበዝ ተኻወት ተጋዳላይ ትግራይ፤
አርኪብካ በሎ ንዚ-ሃሻ አምሃራይ!
ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» በማለት እየተቀኙበት ሊያጠፉት ታፍለው ሳለ የጎንደርና የጎጃም፤ የወሎና የሸዋ ህዝብ ግን መንገድ እያሳዬ፣ «የጠላቴ ጠላት ወዳጄ ነው» ብሎ አብሯቸው እየተዋደቀ፤ ቋንጣና ቆሎ እያዘጋጀ አዲስ አበባ ሚንልክ ቤተ መንግስት ድረስ አጅቦ የሚጠፋበትን በትረ ስልጣን ያስረከበው ራሱ ሆዳሙ አማራ ነው።

ወያኔዎች ስልጣን ከያዙ በኋላም «ሆድ ሲያውቅ ዶሮ ማታ» እያለ ሊታደጉት የተነሱትን ፕሮፌሰር አስራትንና መሰል የህዝብ ልጆችን ቁጭ ብሎ እያየ በወያኔ ያስገደለው እሱ ራሱ አማራው ነው። ከዚያም አልፎ አማሮች እንደ አውሬ ባገራቸው እየታደኑ ሲገደሉ «ወያኔ ከሰራው የአማራ ክልል ውጭ ያሉ አማሮችን አላውቅም» ሲል የወያኔው ሹመኛ፣ ሆዳሙ አማራ ግን በተለመደው የሰነፍ ፍልስፍናው አይቶ እንዳላዬ፣ ሰምቶ እንዳልሰማ የሆነው ራሱ ሆዳሙ አማራ ነው።

ይህ ሆዳም ዝህብ ሊታደጉት ካብራኩ የወጡ ልጆቹን ሁሉ አሳልፎ ለወያኔ በመስጠት አስበልቶ ሲያበቃ የት እንደወደቁ እንኳ ሳይጠይቅ ገዳዩ የመለስ ዜናዊ ሲሞት ግን፣ ኩታውን አዘቅዝቆ፣ ፊቱን ፈጅቶ፣ ደረቱን እየደቃ ከእለት እስካርባ ሀዘን ተቀምጦ የጨካኙን ተስካር ድል አድርጎ ደገሰ። ዛሬ የሚጮህለት ያጣውም ጠላቶቹን አልቅሶ ሲቀብር ለተቆርቋሪዎቹ አንድ ዘለላ እንባ እንኳ በመንፈጉ ነው። ስለዚህ አማራው እያለቀ ያለው ሆዳሙ አማራ በሰራው ስህተቱ ነው። በዚህም የተነሳ ዛሬ ለራሱም ለኢትዮጵያም ሸክምና Helpless Creature ሆኗል። በየእስር ቤቱ አማሮችን ሱሪያቸውን እያስፈቱ «አማራው ሱሪውን መፍታቱን እንድታውቅ ነው» እያሉ ሲሳለቁባቸው፤ ዘሩን እንዳይተካ የአማራ ወንድ በየማጎሪያው ሲኮላሽ፤ እናቶች የሚያመክን መርፌ ሲወጉ ሆዳሙ አማራ ግን ምንም እንዳልደረሰበት አይቶ እንዳላየ የዝምታ ግርማ ውስጥ ተዘፍቆ ይኖራል።

አውቃለሁ ይህንን በመናገሬ «አድጊ፣ አሻ፣ ጓሀፍ» እያሉ በፎከሩበት፤ «ገረብ ገረብ ትግራይ መቃብር አምሃራይ» በማለት ታጋዮቻቸውን ያጀገኑትን፤ «ጎበዝ ተዓወት ተጋዳላይ ትግራይ፣ አርኪብካ በሎ ንዚ ዓሻ አምሃራይ፤ ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» በማለት ያጠፉትን ወያኔችን አንድም ያልተነፈሰ ሆዳም አማራ ሁሉ በእኔ ላይ እንደሚነሳ ይገባኛል። የአማራው ጠላት ሆዳሙ አማራ እንደሆነ ስለማቅ ግን ማንም ሆዳም እየተነሳ በበላበት ቢጮህ አይገደኝም።

ሰው የሌለው የጎንደር መሬት ግን እንዲህ እያለ ይጮሃል…..

መተማ ሁመራ ቋራም ሆድ ሲብሰው፣
ሱዳን ተሰደደ መሬቱም እንደሰው፤

የፕሮፌሰር አስራት ልጅ የሆነው የጎንደር ገበሬም ብቻውን ያለሰው ያለዘር ቢጮህ ምን ያደርጋል ብሎ እንዲህ ይላል….

በሮቼን አምጡልኝ አርጀ ልብላቸው፣
ደግሞ እንደመሬቱ ሳይቆረጥማቸው፤
መሬቱን ሲያርሱብኝ እያየሁ ዝምብዬ፣
ዘር ሳይዙ ማረስ ምን ያደርጋል ብዬ፤
እንዲህ ያለ ዘመን የተገላቢጦሽ፣
አህያ ወደ ቤት ውሻ ወደ ግጦሽ።
===================================================

የግርጌ ማስታወሻ
*«ገረብ ገረብ ትግራይ፣
መቃብር አምሃራይ!»
ትርጉም በግርድፉ:- የትግራይ ተራሮች የአማራ መቃብር ይሆናሉ

*«ጎበዝ ተኻወት ተጋዳላይ ትግራይ፤
አርኪብካ በሎ ንዚ-ሃሻ አምሃራይ!
ጅግና ተጋዳላይ ስማ’እሞ ህዝባዊ ሰራዊት ስማ’እሞ………………..» እያሉ

ትርጉም:- ጎበዝ ድል አድርግ የትግራይ ተጋዳላይ፤ ተከትለህ በለው ይህን ጅል አማራይ

* « አማራ አድጊ፣ አማራ አሻ፣ አማራ ጉሀፍ »
ትርጉም :- አማራ አህያ፣ አማራ ጅል፣ አማራ ቆሻሻ
===================================================

ለሆዳሙ አማራ የተላለፈ ጥሪ እነሆ! ይህን ዝግጅት የግድ መደመጥ ያለበት ነው። ኢሳት ምስጋና ይገባዋል! ወንድማገኝ ተባረክ!

http://ethsat.com/…/esat-tikuret-wondimagegne-discussed-wi…/