Hiber Radio Interview with Chairman of Ethiopia Border Committee

የኢትዮጵያ ድንበር ለሱዳን ተላልፎ ሊሰጥ ጫፍ ላይ የደረሰ ይመስላል። የአገዛዙ <<ጠቅላይ>> ሚኒስትር አቶ ሀይለማርያም ደሳለኝ ባለፈው ወር ይሄንኑ ተግባራዊ የሚያደርግ ስምምነት ካርቱም ላይ ተገኝተው ፈርመዋል። ሕወሃት በትጥቅ ትግል ወቅት ወደ ስልጣን ለመውጣትና ከወጣም በሁዋላ በዛ በኩል ለስልጣኑ የሚያሰጉት እንዳይመጡ በአገር ጥቅም እስከመደራደር፣ አሳልፎ እስከመስጠት እየሄደ ነው የሚል ጠንካራ ስሞታ ይቀርባል። አቶ ሀይለማሪያም ሰሞኑን በኢትዮጵያውያን በኩል ይሄን ሩጫቸውን በመቃወም የአገራችንን ድንበር አትስጡ የሚል ወቀሳ ለማጣጣል ከመሞከር አልፈው <<ተቆርሶ የሚሰጥ መሬት የለም>> ከማለት አልፈው ለሱዳን ጥብቅና ቆመዋል። በዚህ ጉዳይ ላይ ኢትዮጵያውያንን በማስተባበር ድንበሩ ተቆርሶ እንዳይሰጥ ላለፉት ዓመታት ድምጹን በየመድረኩ የሚያሰማው የኢትዮጵያ የድንበር ጉዳይ ኮሚቴ ምላሽ አለው ። ከአቶ አለሙ ያይኔ የኮሚቴው ሊቀመንበር ጋር ቆይታ አድርገናል።

%d bloggers like this: