የአማራ ንቅናቄ ሻእቢያ አመራሮቼን አግቶ ሰውሮብኛል ሲል በድጋሚ ከሰሰ

By MINILIK SALSAWI

ኤርትራ ውስጥ ተቀምጦ በትጥቅ ትግል ነጻነት ይገኛል ብሎ ስለማያስብ ወሳኝ ሃይሉን ከኤርትራ ያስወጣው አማራ ንቅናቄከማንም አስመራ ከመሸገ ድርጅት ጋር ውህደትም ሆነ ትብብር አለመፍጠሩን እና ከሻእቢያ ቁጥር ውጪ ካልወጣን በስተቀር ውህደትም ይሁን አስመራ ተቀምጦ የኢትዮጵያ ህዝብ ነጻነት አይታሰብም ሲል ተደምጧል::
የኤርትራ መንግስት በህገወጥ ሁኔታ ያገታቸውን እና የስወራቸውን ታጋዮቻችንን በአስቸኳይ እንዲለቅ ሲል የአማራ ንቅናቄ ጠየቀ:: የአማራ ንቅናቄ የሚከተሉት በሻእቢያ አመራሮቹ ታፍነው ተወስደዋል ሲል በድጋሚ አስታወቀ::በዚህም መሰረት:
1ኛ – ታጋይ ዳዊት ተሰማ የድርጅቱ ም/ሊቀመንበር እና የፖለቲካ ጉዳዮች ሃላፊ
2ኛ – ታጋይ መላኩ ውብነህ (ሳሚ) የድርጅቱ የትምህርት እና ስልጠና ሃላፊ
3ኛ – ታጋይ ጌትነት አድማሱ (ጃናሞራ) የሻምበል አዛዥ
4ኛ – ታጋይ አስማማው ሙሃባው የሎጀስቲክ እና አቅርቦት ሃላፊ
5ኛ – ታጋይ መሳይ ጥላሁን (ዳሞት) የሻምበል አዛዥ

image

image

%d bloggers like this: