ማኅበረ ቅዱሳን ታገደ

HARA ETHIOPIA ሐራ ዘኢትዮጵያ

image

ማኅበረ ቅዱሳን ታገደ፣የማህበሩ አባላት የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ዕጣ ይደርሰዋል ተብሎ ይጠበቃል
ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ ከ አዲስ አበባ ሀ/ስብከት የለቀቁት በ ወያኔ የደህንነት ኃይሎች በደረሰባቸው ማስፈራራት ነው ተባለ። ማተብ በጥሱም የሚል አዋጅም በ ወያኔ ታውጁዋል።
በወያኔው ፓትርያርክ አቶ ማትያስ ፊታውራሪነት ከተለያየ አድባራት እና ገዳማት የመጡት ጥቂት በጥቅም የተገዙ የደብር አለቆች፣ የጠቅላይ ቤተ ክህነት መምሪያ ሃላፊዎች፣የ አዲስ አበባ ሀገረስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተብሎ በወያኔ የተሾመው ኦህዴድን ወክሎ ወያኔ ፓርላማ ተመራጭ የሆነው አቶ በላይ መኮንን፣ንቡረ እድ ኤልያስ ኣብርሃ የሚመራውና አባ ሰረቀ ብርሃን ወልደ ሳሙኤል፣ መጋቤ ካህናት ኃይለ ሥላሴ ዘማርያም፣ መዝገበ ጥበብ ቀሲስ ዮሐንስ ኤልያስ፣ኤልያስ አብርሃ እንዲሁም ሊቀ ትጉሃን ዘካርያስ ሐዲስ ያሉበት ቡድን ከ ሚኒስትር ዶ/ር ሺፈራው ጋር በመሆን ባቀነባበሩት ክስ ማህበሩን ወደ ማገድ እና በ አሸባሪነት የማስወገዝ ደረጃ ተሸጋግረዋል ።

የጎዳና ላይ ነውጥ ለማነሣሣት ሁከትና ብጥብጥ የሚሰብኩና የሁከትና ብጥብጥ መንገድን የሚቀይሱ ግለሰቦችና ቡድኖች የተሰባሰቡበት ነው በሚል የሀሰት ክስ የመታገድ እርምጃ የተወሰደበት ማኅበረ ቅዱሳን እስካሁን ያወጣው ምንም አይነት መግለጫ የለም። የማህበሩ የጂማ ንዑስ ማዕከል እና የዋናው ማእከል አንዳንድ አመራሮች እና አባላት ባለፉት ሁለት ቀናት በወያኔ የ ፅጥታ ኃይሎች ማዋከብ እና ፍተሻ እየተካሂደባቸው ቢሆንም ምንም አይነት መረጃ ለሚድያ እንዳይሰጡ በማህበሩ ዋና ፀሐፊ አቶ ተስፋዬ ቢሆነኝ እንደተነገራቸው ለማወቅ ተችሉዋል ። ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ታዛቢወች ማህበሩ ለ ቤተ-ክርስቲያኒቱ ትልቅ አስተዋፅኦ እያደረገ ቢሆነም የማህበሩ ጥቂት አመራሮች ግን ከወያኔ ጋር በመተባበር አሁን በ ወያኔ የተሾሙተን አቶ ማትያስ ከማስመረጥ ጀምሮ ከበስደት ሀገር ከሚገኘው በብፁዕ አቡነ መርቆርዮስ ከሚመራው ሕጋዊው ሲኖዶስ ጋር ይደረግ የነበረውን የአባቶችን የእርቅ ውይይት እስከ ማስተጉዋጎል ድረስ አፍራሽ ሚና ይጫወት እንደነበር አስታውሰዋል ። በአሁኑ ሰዓት ወያኔ በሀገራቺን ላይ እያደረሰ ያለው ግፍ ፅዋውን ሞልቶ እየፈሰስ ይገኛል ። በ ወንዶምቻችን የኢትዮጵያ ሙስሊሞች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎች ላይ ያደረገውን የሐሰት ክስ አሁንም በማህበረ ቅዱሳን ላይ ሊደግመው ዝግጅቱን አጠናቆ ይገኛል ።

http://haraethiopiadotcom.wordpress.com/

%d bloggers like this: